Bible Interpretation, Amharic Mentor Guide

/ 1 3

የመጽሐፍ ቅዱስ ሥነ-አፈታት

መጽሐፍ ቅዱሳዊ እስትንፋሰ እግዚአብሔር የመጽሐፍ ቅዱስ አመጣጥና ሥልጣን

ትምህርት 1

ገጽ 291  1

ሃያል በሆነው በጌታ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ሰላም ለአንተ ይሁን ! የዚህን ትምህርት መጽሐፍ ካነበብክ፥ ካጠናህ፥ ውይይት ካካሄድክና ወደ ተግባር ከቀየርከው በኋላ የሚከተሉትን ማድረግ ትችላለህ:- • ስነ አፈታትን እንደ አንድ በትርጓሜ ላይ፣ በተለይም በምንባቦች ትርጓሜ ላይ እንደሚያተኩር የጥናት እና የእውቀት ዘርፍ መግለጽ ትችላለህ፣ ። • የመጽሐፍ ቅዱስን ምንነት ለመገንዘብና ሙሉ በሙሉ ለመረዳት መጽሐፍ ቅዱስ መለኮታዊና ሰዋዊ መጽሐፍ እንደሆነ ተደርጎ መተርጎም እንዳለበት ማስረጃ ትሰጣለህ። • ስለ ቅዱሳት መጻሕፍት መለኮታዊ መምጫቸው፣ ቅዱሳት መጻሕፍትን መተርጎም፣ ሂደታዊ የመገለጥ ሀሳብ፣ በክርስቶስ ላይ ያተኮረ የመጽሐፍ ቅዱስ ተፈጥሮ እና የእግዚአብሔርን ቃል ለመረዳት የመንፈስ ቅዱስ አስፈላጊነት ጨምሮ በታሪካዊ ኦርቶዶክሳዊ ክርስቲያኖች ስለ ቅዱሳት መጻሕፍት ተፈጥሮ ያመኑትን ወሳኝ ቅድመ-ሁኔታዎች ማብራራት ትችላለህ። • የመጽሐፍ ቅዱስ ትርጓሜን የሶስት ደረጃ ሞዴል አጠቃላይ እይታ ትሰጣለህ፣ ይህም የቀደመውን ሁኔታ መረዳትን፣ የመጽሐፍ ቅዱስ መርሆችን መመርመርን እና የመጽሐፍ ቅዱስን ትርጉም በሕይወታችን ላይ ተግባራዊ ማድረግን ያካትታል። • ለመጽሐፍ ቅዱስ ትርጓሜ ልብን ለማዘጋጀት የሚያስፈልጉትን የተለያዩ ነገሮች ማለትም ትሕትናንና ጸሎትን፣ ትጋትንና ቁርጠኝነትን እንዲሁም መጽሐፍ ቅዱስን እንደ ትጉህ ሰራተኛ በጥንቃቄ ማጥናት አስፈላጊ መሆኑን መግለጽ ትችላለህ። • አእምሯችንን ለትልቅ የመጽሐፍ ቅዱስ ትርጓሜ ስናዘጋጅ ሊኖረን ስለሚገባው ሚና ግንዛቤ እንዳለህ ማሳየት ትችላለህ፤ ይህ ሚና ደግሞ ቃሉን በትጋት መፈለግ፣ ፍንጮችን በመከተል እንዲሁም ማስረጃዎቹን በጥንቃቄ በመመዘን ውሳኔ ከማስተላለፍህ በፊት የመመርመርን ሚና ይጨምራል። • መጽሐፍ ቅዱስ በእግዚአብሔር መንፈስ አነሳሽነት የተጻፈ ከመሆኑም በላይ በሰዎች የተጻፈ መሆኑን ከቅዱሳት ጽሑፎች በመነሳት ማስረዳት ትችላለህ። • ቅዱሳት መጻሕፍት በመንፈስ ቅዱስ እንዴትና በምን መንገድ እንደተጻፉ እንዲሁም እንዴት በጸሐፊዎቹ ሰዎች ተጽዕኖ እንደተደረገባቸው ለመግለጽ የሚጥሩትን የተለያዩ የመንፈስ አነሳሽነት ንድፈ ሐሳቦች መግለጽ ትችላለህ። • ምክንያታዊ እና ታሪካዊ መጽሐፍ ቅዱሳዊ ትችት በጥንቃቄ ማቅረብ ትችላለህ፤ እንዲሁም ይህ ዘመናዊው ትችት እንዴት የመጽሐፍ ቅዱስን አመጣጥ በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ከተጠቀሱት የመጀመሪያዎቹ ክስተቶች አንስቶ በመጽሐፍ ቅዱስ ቀኖናዊ መጻሕፍት ውስጥ እስከተዘገቡት ክስተቶች ድረስ በመከታተል እንደሚያዛምድ ማሳየት ትችላለህ።

የትምህርቱ አላማ

ገጽ 293  2

1

Made with FlippingBook flipbook maker