Bible Interpretation, Amharic Mentor Guide
2 8 /
የመጽሐፍ ቅዱስ ሥነ-አፈታት
IV. በመጽሐፍ ቅዱስ ትርጓሜ የፈቃዱ ዝግጅት አስፈላጊነት፡ የእግዚአብሔርን ቃል ለመለማመድ ራስህን ዝግጁ አድርግ።
ሀ. የቃሉ አድራጊ ሁን፣ ያዕ 1፡22-25፣ ዝከ. ዕዝራ 7፡10
1. የእግዚአብሔርን ቃል በምታጠናበት ጊዜ የጌታን ድምፅ ስማ፣ ዕብ. 3.7-13.
2. የእግዚአብሔርን ማነሳሳት ወዲያውኑ አድርግ።
1
3. ለሌሎች የማንበብ ልማድ አይንርህ፣ እና እግዚአብሔር ለራስህ ሲናገር ለመስማት አንብብ
4. የእግዚአብሔር ቃል በጥናት ልማድህ ላይ ብቻ ሳይሆን በሕይወትህም ላይ ተጽዕኖ እንዲያሳድር ጠብቅ።
ለ. ጥበብ የሚገኘው የእግዚአብሔርን ቃል በመታዘዝ እንጂ በመተርጎም ብቻ አይደለም፣ መዝ. 111.10.
1. ጠንካራ የመጽሐፍ ቅዱስ ሊቃውንት ቃሉን ለማጥናት አይኖሩም ይልቁንም ለመኖር ይማራሉ ።
ሀ. ዘዳ. 4.6
ለ. ኢያሱ 1፡7-8
2. ማስተዋል የሚከሰተው የእግዚአብሔርን ቃል በማሰላሰላችን እንጂ ማስታወሻዎች እና ማብራሪያዎችን በመስጠታችን ብቻ አይደለም፣ መዝ. 119.98-101.
Made with FlippingBook flipbook maker