Church PLANT Manual, Amharic Edition
36 • የቤተ ክርስቲያን ተከላ መምሪያ
መልመጃ 4 ተግዳሮቶችን የመቋቋም ዐቅምን ማጐልበት
ቤተ ክርስቲያን ለመትከልና ለመምራት በጋራ ስትሠሩ ቡድናችሁ ጤናማ የሆነ የአገልግሎት ሥርዓተ ጥለቶችን መመሥረት ይኖርበታል። ቤተ ክርስቲያን ተከላ አካላዊ፣ ስሜታዊና መንፈሳዊ መሰጠቶችን የግድ እንደሚልና በጋራ ጤናማ የሆኑ ንድፎችን ማዘጋጀት እንዴት እንደምትችሉ ቡድናችሁ ማወቅና መመካከር አለበት። መመሪያዎች ከዚህ በታች በቀረቡት ጥያቄዎች ዙሪያ ጤናማ የአገልግሎት ንድፎችን እንደ ቡድን በጋራ እንዴት መቅረጽ እንደምትችሉ ጊዜ ወስዳችሁ ተወያዩ። 1. በቡድናችሁ ውስጥ ቅድሚያ ሰጥታችሁ ልታዳብሯቸው የሚገቡ በተለያዩ ጊዜያት ሊደረጉ የሚችሉ መንፈሳዊ ተግባራት (ሰንበት፣ ጸሎት፣ ጾም፣ በቃሉ ውስጥ ለመሆን ጊዜ መውሰድ) ምንድን ናቸው? 2. ቡድናችሁ እንዴት ባለ መልኩ ጤናማ ቤተ ሰባዊ ከባቢን መደገፍና ማበረታታት ይችላል? 3. ቡድናችሁ ጤናማ መንፈሳዊና ቤተ ሰባዊ ከባቢን ለመፍጥር፣ ለመደገፍና ለማበረታት የተመደቡት ሰዎች ምን ዐይነት ሰዎች ናቸው? እንደዚህ ዐይነት ሰዎች ቡድናችሁ ከሌለው ድጋፍ በመስጠት ማደግ የምትችሉት እንዴት ነው? 4. ለቡድናችሁ የሚጠቅሙ ሥልጠናዎች ወይም መሣሪያዎች ይኖሩ ይሆን? 5. ተግዳሮቶችን መቋቋምን ማጐልበት በሚለው ትምህርት መሠረት መለወጥ ያሉብን ነገሮች ይኖሩ ይሆን?
Made with FlippingBook - Share PDF online