Conversion and Calling, Amharic Student Workbook

/ 1 0 9

ለ ው ጥ እ ና ጥ ሪ

መ. በክርስቶስ ያለንን ነፃነታችንን እንድንጠቀም የተጠራንባቸው አላማዎች።

1. ለሚጠቅመው ነገር፣ 1ኛ ቆሮ. 6፡12 ሀ - “ሁሉ ተፈቅዶልኛል፣ ሁሉ ግን አይጠቅምም።”

2. ለማንኛውም ጎጂና ሱስ የሚያስይዝ ነገር አይደለም፣ 1ኛ ቆሮ. 6፡12 ለ - “ሁሉ ተፈቅዶልኛል፥ በእኔ ላይ ግን አንድ ነገር እንኳ አይሠለጥንብኝም።”

3. የሚያንጽ ብቻ ነው፣ 1ኛ ቆሮ. 10፡23 - “ሁሉ ተፈቅዶልኛል፥ ሁሉ ግን የሚጠቅም አይደለም፤ ሁሉ ተፈቅዶልኛል፥ ነገር ግን ሁሉ የሚያንጽ አይደለም።”

4. ደካማ አማኝን የሚያሰናክል ማንኛውም ነገር አይደለም፣ 1ኛ ቆሮ. 8፡13 - “ስለዚህም መብል ወንድሜን የሚያሰናክለው ከሆነ፥ ወንድሜን እንዳላሰናክለው ለዘላለም ከቶ ሥጋ አልበላም።”

5. በጌታ ወንድሞቻችንን እና እህቶቻችንን ለመውደድ እድል ለሚሰጡ ነገሮች ብቻ፣ ገላ. 5፡13 - “ወንድሞች ሆይ፥ እናንተ ለአርነት ተጠርታችኋልና፤ ብቻ አርነታችሁ ለሥጋ ምክንያትን አይስጥ፥ ነገር ግን በፍቅር እርስ በርሳችሁ እንደ ባሪያዎች ሁኑ።”

4

6. እግዚአብሔርን ለሚያከብሩ ነገሮች ብቻ፥ 1ኛ ቆሮ. 10፡31 - “እንግዲህ የምትበሉ ወይም የምትጠጡብትሆኑ ወይምማንኛውንም ነገር ብታደርጉ ሁሉን ለእግዚአብሔር ክብር አድርጉት።

7. አይሁድን፣ አሕዛብን፣ ወይም የእግዚአብሔርን ቤተ ክርስቲያን ለሚያስቆጣ ማንኛውም ነገር አይደለም፣ 1ኛ ቆሮ. 10፡32 - “ለአይሁድም ለግሪክም ሰዎች ለእግዚአብሔር ቤተ ክርስቲያንም ማሰናከያ አትሁኑ።”

8. ሌሎችን ወደ ክርስቶስ ለማሸነፍ ለሚረዱት ነገሮች ብቻ፣ 1ኛ ቆሮ. 10፡33 - “እኔ ደግሞ ብዙዎቹ ይድኑ ዘንድ ለጥቅማቸው እንጂ የራሴን ጥቅም ሳልፈልግ በሁሉ ነገር ሰውን ሁሉ ደስ እንደማሰኝ፥”

Made with FlippingBook - Online magazine maker