God the Father, Amharic Mentor Guide

/ 1 0 3

እግዚአብሔር አብ

እግዚአብሔር እንደ አባት የእግዚአብሔር ቸርነት

ትምህርት 4

ገጽ 273  1

የትምህርቱ ዓላማዎች

ሃያል በሆነው በጌታ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ሰላም ለአንተ ይሁን ! የዚህን ትምህርት (ሞጁል) መጽሐፍ ካነበብክ፣ ካጠናህ፣ ውይይት ካካሄድክና ወደ ተግባር ከቀየርከው በኋላ የሚከተሉትን ማድረግ ትችላለህ:- • በፍጹም የሞራል ንጽህናው፣ ፍፁም ንጹሕ አቋሙ እና ገደብ የለሽ ፍቅሩ በሥነ ምግባራዊ ባሕርያቱ ውስጥ የተገለጸውን የእግዚአብሔርን አስደናቂ መልካምነት መግለጫ መስጠት። • የእግዚአብሔር ፍጹም ሥነ ምግባራዊ ንጽሕና በቅድስናው፣ በጽድቁ እና በፍትህ እንዴት እንደሚገለጥ ማሳየት። • ከእግዚአብሔር ፍጹም አቋም ጋር የተያያዙትን እነዚህን ባሕርያት ማለትም የእሱ እውነተኛነት፣ ትክክለኛነት እና ታማኝነት ግልጽ ማድረግ። • ከእግዚአብሔር ፍቅር፣ ቸርነቱ፣ ጸጋው፣ ምሕረት እና ጽናት ጋር የተቆራኙትን ባህሪያት ጠቅለል አድርገህ ማቅረብ። • የእግዚአብሔርን ቁጣ መጽሐፍ ቅዱሳዊ መሠረት ከሥነ ምግባራዊ ባሕርዩ ጋር በተያያዘ መግለጽ። • በእግዚአብሔር ቸርነት እና ቆራጥነት፣ በፍቅሩ እና በፍትህ መካከል ያለውን ግንኙነት ማስረዳት። • ስለ ጌታ እና ስለ ድርጊቶቹ ማንኛውንም ግራ መጋባት ወይም ግጭት የሚከላከል የእግዚአብሔርን ባህሪያት እና ተፈጥሮ መረዳት እንደሚያስፈልግ መግለጽ። እባክህ ራስህን አታሞኝ ሮሜ. 2፡3-11 - አንተም እንደዚህ በሚያደርጉ የምትፈርድ ያንም የምታደርግ ሰው ሆይ፥ አንተ ከእግዚአብሔር ፍርድ የምታመልጥ ይመስልሃልን? [4] ወይስ የእግዚአብሔር ቸርነት ወደ ንስሐ እንዲመራህ ሳታውቅ የቸርነቱንና የመቻሉን የትዕግሥቱንም ባለጠግነት ትንቃለህን? [5] ነገር ግን እንደ ጥንካሬህና ንስሐ እንደማይገባ ልብህ የእግዚአብሔር ቅን ፍርድ በሚገለጥበት በቍጣ ቀን ቍጣን በራስህ ላይ ታከማቻለህ። [6] እርሱ ለእያንዳንዱ እንደ ሥራው ያስረክበዋል፤ [7] በበጎ ሥራ በመጽናት ምስጋናንና ክብርን የማይጠፋንም ሕይወት ለሚፈልጉ የዘላለምን ሕይወት ይሰጣቸዋል፤ [8] ለዓመፃ በሚታዘዙ እንጂ ለእውነት በማይታዘዙትና በአድመኞች ላይ ግን ቍጣና መቅሠፍት ይሆንባቸዋል። [9] ክፉውን በሚያደርግ ሰው ነፍስ ሁሉ መከራና ጭንቀት ይሆንበታል፥ አስቀድሞ በአይሁዳዊ ደግሞም በግሪክ ሰው፤ [10] ነገር ግን በጎ ሥራ ለሚያደርጉ ሁሉ ምስጋናና ክብር

4

ጥሞና

ገጽ 274  2

Made with FlippingBook - Online magazine maker