Bible Interpretation, Amharic Mentor Guide

/ 1 7

የመጽሐፍ ቅዱስ ሥነ-አፈታት

ያጎላሉ። የመጽሐፍ ቅዱስ ትርጓሜ ውስጥ በመጽሐፍ ቅዱስ የአተረጓጎም ዘዴ እና የመጽሐፍ ቅዱስ ባለቤት በሆነው የመንፈስ ቅዱስ ሥራ መካከል ያለው ግንኙነት ምንድን ነው? ምንም እንኳን ጥሩ የስነ አፈታት ዘዴዎች ቢኖሩንም ያለ መንፈስ ቅዱስ ብርሃን መጽሐፍ ቅዱስን ትርጉም ባለውና ሕይወትን በሚቀይር መንገድ መረዳት ይቻላልን?

ሥነ ጽሑፍ ወይስ ሕያው የእግዚአብሔር ቃል ወይስ ሁለቱም? ባለፉት ጥቂት አሥርት ዓመታት ውስጥ የተወሰኑ ምሁራን መጽሐፍ ቅዱስን እንደ ሥነ ጽሑፍ መረዳት ለሕይወታችን ያለውን ትርጉም ለማወቅ እንደሚያስፈልግ አበክረው ተናግረዋል። የሥነ ጽሑፍ ሥራ መጽሐፍ ቅዱሳዊ ሆነም አልሆነ የሚከናወነው በተመሰረቱ ህጎችና ቅርጾች እንደሆነ ይሞግታሉ። እነዚህ ምሁራን መጽሐፍ ቅዱስን እንደ ሰዋዊ መጽሐፍ ባለው ቅርጽና ህጎች መሰረት ከማንበብ ይልቅ መጽሐፍ ቅዱስን ወደ ትንንሽ ክፍሎች ቆርጠን እንደወሰድነው፣ የሥነ ጽሑፍ ዓይነቶችን ችላ እንዳልን፣ እና መጽሐፍ ቅዱስን በዋናነት እንደ ማስረጃ ተጠቅመን አንድን ወይም ሌላን ሥነ-መለኮታዊ ርዕሰ ጉዳይ ለመሞገት እንደሞከርን ይናገራሉ። አንዳንዶች ደግሞ መጽሐፍ ቅዱስን የጻፉት ሰዎች ቢሆኑም ጽሑፎቹ ከሥነ ጽሑፍ ደንቦችና ቅርጾች ያለፉ እንደሆኑ ይናገራሉ። መጽሐፍ ቅዱስ በኢየሱስ ክርስቶስ አማካኝነት ስላገኘነው ድነት እና እምነትን በተመለከተ ትርጓሜን ሊሰጠን የሚችል የሕያው የእግዚአብሔር ቃል እንደሆነ ይሞግታሉ። ለእንደዚህ አይነቱ ሙግት የአንተ ምላሽ ምን ሊሆን ይችላል? መጽሐፍ ቅዱስ የሥነ ጽሑፍ መጽሐፍ ነው ወይስ የሕያው የእግዚአብሔር ቃል? ወይስ ሁለቱንም?

3

1

የመጽሐፍ ቅዱስ እስትንፋሰ እግዚአብሔር፡ የመጽሐፍ ቅዱስ አመጣጥ እና ሥልጣን ክፍል 1፡ ጠጠር ላለ መጽሐፍ ቅዱሳዊ ትርጓሜ መዘጋጀት

ይዘት

ቄስ ዶክተር ዶን ኤል ዴቪስ

ስነ አፈታት በትርጓሜ ላይ፣ በተለይም በምንባቦች ትርጓሜ ላይ የሚያተኩር የጥናት እና የእውቀት ዘርፍ ነው። ሂርሜኔዩቲክስ እንደ ስነ አፈታት ዘዴ መጽሐፍ ቅዱስን እንደ መለኮታዊ እና እንደ ሰዋዊ መጽሐፍ ለመተርጎም መሄድ ስላለበት መንገድ ለመረዳት ይፈልጋል፣ የቅዱሳት መጻሕፍትን ተፈጥሮ ለመገንዘብ እና ሙሉ በሙሉ ለመረዳት ሁለቱም ልኬቶች ያስፈልጋሉ። ታሪካዊ ኦርቶዶክሳውያን ክርስቲያኖች ከመጀመሪያው ጀምሮ በቅዱሳት መጻሕፍት ተነሳሽነት፣ ቅዱሳት መጻሕፍትን በቅዱሳት መጻሕፍት የመተርጎም አስፈላጊነት እና በክርስቶስ መገለጥ ስለሚጠናቀቅ ሂደታዊ የመገለጥ ሀሳብ ያምናሉ። ቅዱሳት መጻሕፍትን መረዳት የሚቻለው በመንፈስ ቅዱስ አማካኝነት ብቻ ነው። የመጽሐፍ ቅዱስ ትርጓሜ የሶስት ደረጃ ሞዴል የመጀመሪያውን ሁኔታ መረዳትን፣ የመጽሐፍ ቅዱስን መርሆች መመርመርን እና የመጽሐፍ ቅዱስን ትርጉም በሕይወታችን ውስጥ ተግባራዊ ማድረግን ያካትታል። የእግዚአብሔርን ቃል በትክክል ለመተርጎም ልባችንን፣ አእምሯችንንና ፈቃዳችንን በማዘጋጀት በትሕትናና በጥንቃቄ ማጥናት፣ በጥንቃቄ መመርመርና ከልብ መታዘዝ ይኖርብናል፤ ይህም ለእግዚአብሔር ክብርን ያመጣል።

የክፍል 1 አጭር ማብራሪያ

Made with FlippingBook flipbook maker