Church PLANT Manual, Amharic Edition

16 • የቤተ ክርስቲያን ተከላ መምሪያ

ትልቅም ይሁን ትንሽ በእያንዳንዱ እንቅስቃሴ ውስጥ የቤተ ክርስታየን ተከላ ቡድናችሁ የጋራ የሆነ ራእይን በተመለከተ ግልጽ የሆነ ግንዛቤና የጋራ አስተዋጽዖ ሊኖረው ይገባል። 2 ግልጽ የሆነ ራእይ “ማድረግ እንችላለን” በማለትና “ማድረግ አለብን” በማለት መካከል ያለውን ልዩነት በግልጽ በመረዳት ውሳኔዎቻችሁ በስሜት፣ በወጪዎች፣ ወይም ባሏችሁ ሀብቶች ላይ የተመሠረቱ እንዳይሆኑ ያስችላችኋል። • በግልጽ በራእያችሁ ላይ አተኩሩ • ለራእዩ አስተዋጽዖ ባላቸው ነገሮች ላይ ብቻ ተጠመዱ • ሊሠሩ የሚችሉ ብዙ መልካም ነገሮች ቢኖሩም ለራእያችሁ አስተዋጽዖ የሚያበረክቱት ጥቂት ናቸው። • ደካማ ባላደራነት በራእይ ሳይሆን በመልካም አጋጣሚዎች እንድንመራ ይዳርገናል። • በጣም ቀላሉን መንገድ ብቻ መምረጥ ሳይሆን የእያንዳንዱን ውሳኔ አንድምታ በጥንቃቄ አጢኑ።

• ስሜታችሁ በቀላሉ ሊያታልላችሁ ስለሚችል “ንቁ አእምሮ ይኑራችሁ፤ ራሳችሁንም የምትገዙ ሁኑ” (1ጴጥሮስ 4፥7)። • ራስን መግዛት የሌለበት ጐዳና ከፍተኛ ዋጋ ያስከፍላል። 3

III.ዋና ዕሴቶቻችሁ ምን እንደሆኑ ወስኑ የሁሉም የቤተ ክርስቲያን ተከላ ቡድኖች ታላቅ ተግዳሮት ሥራቸውን የሚመሯቸውን ዕሴቶች መወሰን ነው። ሌሎች ዕሴቶች ጠቃሚ ቢሆኑም እንኳ የትኛዋም ቤተ ክርስቲያን እያንዳንዱ የቡድኑ አባል የሚያመጣውን ዕሴት ሁሉ ምርጥ አድርጋ መሸከም አትችልም። የእናንተ ቡድን ከራእያችሁ ጋራ የሚገጥሙ የጋራ ዕሴቶቻችሁ ምን እንደሆኑ መወሰን አለበት። የትኛዋም ቤተ ክርስቲያን ዐሥር ነገሮችን

2 3

Ripe for Harvest , p. 44 Ripe for Harvest, p. 67.

Made with FlippingBook - Share PDF online