Church PLANT Manual, Amharic Edition
መግቢያ • 3
የቤተ ክርስቲያን ተከላ መጽሐፍ ቅዱሳዊ መሠረቶች ሬቨረንድ ቴድ ስሚዝ
ብዙውን ጊዜ “ዓለም አቀፋዊት” 1 በመባል የምትጠራውን ቤተ ክርስቲያኑን ጌታ እንዲሠራ (ማቴዎስ 16፥18) እንዲሁም ጌታ ራሱ “አካሉ የኾነችው የቤተ ክርስቲያን ራስ” መኾኑን (ቆላስይስ 1፥18) መጽሐፍ ቅዱስ በግልጽ ይናገራል። ስለዚህም ቤተ ክርስቲያን የመትከል ተግባር ሙሉ በሙሉ “ስለዚህ ሂዱና ሕዝቦችን ሁሉ በአብ፣ በወልድና በመንፈስ ቅዱስ ስም እያጠመቃችኋቸው ደቀ መዛሙርት አድርጓቸው፤ ያዘዝኋችሁንም ሁሉ እንዲጠብቁ አስተምሯቸው፤ እኔም እስከ ዓለም ፍጻሜ ድረስ ሁልጊዜ ከእናንተ ጋር ነኝ” (ማቴዎስ 28፥19-20) በሚለው የክርስቶስ ሥልጣንና ትእዛዝ ላይ የተሠረተ ነው። ይኹን እንጂ ዛሬ ቤተ ክርስቲያናትን ለመትከል የሚተጉ ሰዎች “ለምን ሌላ ቤተ ክርስቲያን ያስፈልገናል? በመላው አሜሪካ ቤተ ክርስቲያናት ሞልተዋል” ሲሉ ይደመጣሉ። ተጨማሪ ቤተ ክርስቲያናት ለምን ያስፈልጉናል? በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ (ከውድቀት ጀምሮ፣ ዘፍጥረት 3፥1-15) “በዓለም ላይ” የዲያብሎስ ተጽዕኖ እንዳለ በግልጽ ይነግረናል። ኢየሱስም፥ “የዚህ ዓለም ገዥ” (ዮሐንስ 12፥31) በማለት ጠርቶታል። ጳውሎስም “በአየር ላይ [ያ]ሉት መንፈሳውያን ኀይላት ገዥ… ለእግዚአብሔር በማይታዘዙት ሰዎች ላይ [የ]ሚሠራው መንፈስ (ኤፌሶን 2፥2)፤ “የዚህ ዓለም አምላክ” (2ቆሮንቶስ 4፥4) ብሎ ጠርቶታል። ዮሐንስም “መላው ዓለምም በክፉው ሥር” እንደ ሆነ ጽፏል። ግልጽ ለማድረግ፥ ዲያብሎስ ከእግዚአብሔር ጋራ እኩል አይደለም። ሁሉን የሚችል ኀያል አይደለም፤ ከኢየሱስ ጋራ ፈጽሞ አይወዳደርም። በሰይጣን ላይ የመጨረሻ ፍርድና ወሳኝ ድል ይኾናል። “ወደ እሳቱና ወደ ዲኑ ባሕር” ተጥሏል “ለዘላለም ይሠቃያል” (ራእይ 20፥10)። የትኛውም ዐይነት መንግሥት እና/ወይም ሥልጣን ሁሉ ከሰይጣን ይወሰዳሉ። ትክክለኛው ባለቤታቸው ለኾነውና ለሚገባው ለንጉሡ ኢየሱስ ተላልፈው
1 ኤክሌሲያ ዩኒቨርሳሊስ የሚለው የላቲን ቃል በመላው ዓለም ያለችውን ቤተ ክርስቲያን ያመለክታል።
Made with FlippingBook - Share PDF online