Church PLANT Manual, Amharic Edition

8 • የቤተ ክርስቲያን ተከላ መምሪያ

የቤተ ክርስቲያን ተከላ ዐሥር መርሖች 5 1. ኢየሱስ ጌታ ነው። (ማቴዎስ 9፥37-38) ሁሉም የቤተ ክርስቲያን ተከላ እንቅስቃሴዎች ውጤታማና ፍሬያማ የሚኾኑት የመኸሩ ጌታ በኾነው በጌታ በኢየሱስ ጥበቃና ኀይል ነው። 2. ስብከተ ወንጌል፣ በወንጌል ያልተደረሱ ሰዎች ሌሎች ሰዎችን ይደርሱ ዘንድ ማስታጠቅና ማበረታታት። (1ተሰሎንቄ 1፥6-8) ሌሎችን ለክርስቶስ የመድረስ ግባችን ለጠንካራ ለውጥ ብቻ ሳይኾን በቀጣይ ይበዙም ዘንድ ነው። በወንጌል የተለወጡ ሰዎች ለሌሎችን በወንጌል ለመድረስ መሠልጠን አለባቸው። 3. አካታች መሆን፥ ማንም ሊመጣ ይችላል። (ሮሜ 10፥12) የትኛውም ስልት ማንም ሰው ወይም ቡድን በኢየሱስ ክርስቶስ በማመን ወደ እግዚአብሔር መንግሥት እንዳይገባ መከልከል የለበትም። 4. ከ ባህል ገለልተኛ መሆን፥ የሆናችሁትን ሆናችሁ ኑ። (ቈላስይስ 3፥11) ወደ ኢየሱስ የሚመጡ ሰዎች ባህላቸውን እንዲቀይሩ ወንጌሉ ቅድመ ኹኔታ አያስቀምጥም። እንደሆኑት ሆነው መምጣት ይችላሉ። 5. የምሽግ አስተሳሰብን ማስወገድ። (ሐዋርያት ሥራ 1፥8) የወንጌል ተልእኮ ዐላማ ባልዳኑ ሰዎች መካከል የማይደፈር ግንብ መገንባት አይደለም። ይልቁንም በዓለም ድንበሮች ሁሉ የኢየሱስ ምስክር የሚሆኑ ደጆችን መክፈት ነው። 6. መቀዛቀዝ እንዳይኖር ስብከተ ወንጌልን መቀጠል። (ሮሜ 1፥16 17) የታላቁን ተልእኮ ራእይ በአእምሯችን ይዘን አድማሱን መመልከት። ለክርስቶስ ደፋር ምስክር የሆነ ከባቢን መፍጠር። 7. የዘር፣ የመደብ፣ የጾታ እና የቋንቋ ድንበሮችን መጣስ። (1 ቀሮንቶስ 9፥19-22) ከቤተ ክርስቲያን በእጅጉ ርቀው ላሉ ሰዎች የመንግሥቱን መልእክት ለማስተላለፍ ዐዳዲስና ተቀባይነት ያላቸውን መንገዶች ለመጠቀም በክርስቶስ ያላችሁን ነጻነት መጠቀም።

5 Mere Missions , Wichita: TUMI Press, 2022. pp 234-236.

Made with FlippingBook - Share PDF online