Church PLANT Manual, Amharic Edition

መግቢያ • 9

8. በማኅበረ ሰቡ ዘንድ ተቀባይነት ያላቸውን ባህሎች ማክበር። (ሐዋርያት ሥራ 15፥23-29) ኢየሱስን ጌታቸውና መዽኀኒታቸው አድርገው በተቀበሉ ሰዎች ቋንቋዎች፣ ልማዶች፣ ዘይቤዎችና ተመክሮዎች ውስጥ ዐልፎ መንፈስ ቅዱስ የእግዚአብሔርን መንግሥት ራእይና ባሕርይ እንዲገልጥ መፍቀድ። 9. ጥገኛነትን ማስወገድ። (ኤፌሶን 4፥11-16) በጣም አነስተኛ በኾነውና እያደገ ባለው የክርስቲያን ማኅበረ ሰብ ውስጥ እንኳ መንፈስ ቅዱስ የእግዚብሔርን ሥራ ከግብ ለማድረስ ያለውን ኀይል አቅልላችሁ አትመልከቱ። 10. ዳግም ተከላ ማሰብ። (2ጢሞቴዎስ 2፥2፤ ፊልጵስዩስ 1፥18) በምትጀምሯቸው እንቅስቃሴዎችና ውጥኖች ሁሉ የወንጌል ተልእኮን ክፍት በሆነ አእምሮ ሌሎች እንዲቀጥሉት ማስታጠቅን ዐስቡ።

Made with FlippingBook - Share PDF online