Church PLANT Manual, Amharic Edition

ቀዳሚ ቃል

ቤተ ክርስቲያኔን እመሠርታለሁ ሰዎች የሚድኑት ወደ መንግሥተ ሰማያት ለመሄድ ብቻ አይደለም። እግዚአብሔር ሰዎችን ይፈጥራል። ይህ ሊጠፋን አይገባም። እንደ አለመታደል ሆኖ ብዙዎች ታላቁን የድነት ታሪክ፣ “እግዚአብሔር ዓለምን ፈጠረ፣ እኛ ኀጢአተኞች ነን፣ ስለዚህ እግዚአብሔር እያንዳንዳችንን ከኀጢአታችን ለማዳን ኢየሱስን ላከው” ወደሚል ቀላል ቀመር አውርደውታል። ፍጥረት፣ ኀጢአት፣ ኢየሱስ ያ ነው መጠቅለያው! አንዳንዶች ታዲያ ይሄ ችግሩ ምንድን ነው? ብለው ይገረማሉ። ችግሩ ይሄ ነው፥ የፍጥረት-ኀጢአት-ኢየሱስ ቀመር በጣም ግላዊ ወደ ሆነ ክርስትና ይመራል፥ እምነታች የግል ሕይወታችን ብቻ እንደሆነ አድርጎ ያቀርባል። ኢየሱስ፥ እኔን፣ ራሴንና እኔን ለማገልገል እንደመጣ የቤተ ክርስቲያንን ደውል ነው። የወንጌሉን መልእክት በእጅጉ አኮስሰነዋል። መጽሐፍ ቅዱስ የሚሰጠን ጥልቅ ታሪክ እንጂ ቀላል ቀመር አይደለም። ኢየሱስ ክርስቶስን ስንመሰክር፥ ክርስቶስ ለኀጢአት ሊሞት መጣ፣ ሰይጣንንና ሥራዎቹ አፈራረሰ፣ እንዲሁም የእግዚአብሔርን መንግሥት አገዛዝ በምድር ላይ ዳግመኛ መሠረተ የሚለውን ዓለምን የሚለውጥ ዐሳብ እያወጅን ነው። ኢየሱስ በሕይወቱ፣ በሞቱ፣ በቀብሩ፣ እና በትንሣኤው ያከናወነው ሥራ ይህን ነው። ከሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ጀምሮ ያሉት የዐዲስ ኪዳን መጻሕፍት በአንዲት አጥቢያ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ

xi

Made with FlippingBook - Share PDF online