Church PLANT Manual, Amharic Edition

xii • የቤተ ክርስቲያን ተከላ መምሪያ

ከሌሎች ክርስቲያኖች ጋራ የሚኖር ክርስቲያንን ታሳቢ ያደረጉ መልእክታት ናቸው። ድነት የግል ነው የሚኖረው ግን በማኅበር ነው። ቤተ ክርስቲያንን ከሌሎች ማኅበራዊ ተቋማት ልዩ የሚያደርጋት ምንድን ነው? የቅድስና ጕዳይ። ቅድስና የድል መንገድ ነው። ኀጢአትን ድል የሚያደርግ እና ለለውጥ የሚያዘጋጅ ጕልበት ሰጪ ነው። የእግዚአብሔር ሕዝብ ያደረገን ይህ ነው። በክርስቶስ ላይ ያለን እምነት ለዚህ አብቅቶናል። ኢየሱስን ከሙታን ያስነሣው ያው ኀይል የተለወጡ ሕይወቶችና ማኅበረ ሰቦች ምንጭ ነው። የሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ የመጀመሪያዎቹ 12 ምዕራፎች የቤተ ክርስቲያን ምሥረታን ታሪክ ይናገራሉ። የመጀመሪያው ቍልፍ ገጸ ባሕርይ ጴጥሮስ ነው። ጴጥሮስ፥ ኢየሱስ የእግዚአብሔር ልጅ እንደሆነ በመሠከረ ጊዜ ቍልፍ የቤተ ክርስቲያን ተካይ እንደሚሆን ኢየሱስ ነግሮት ነበረ (ማቴዎስ 16፥18)። ከትንሣኤው በኋላ፥ ኢየሱስ ከተከታዮቹ ጋራ 40 ቀናት አሳልፏል። በእነዚህ ጊዜያት የመንፈስ ቅዱስ ኀይል ምንጭ ተገልጦ ነበረ። ኢየሱስ ስለ እግዚአብሔር መንግሥትና ሁሉም አማኞች ሁሉ የመንግሥቱ ዜጎች ሆነው መኖር እንዳለባቸው አስተምሯል። ይህ እንዲሆን ያስቻለው የመንፈስ ቅዱስ ሀልዎት ነበረ። ርሱ ዳግመኛ ተመልሶ እስኪመጣና ክፈን ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ እስኪደመስስ ድረስ መንግሥቱ እንደማትመጣ ተናግሮ ነበረ። እስከዚያ ድረስ ሁሉም የርሱ ተከታዮች በአጥቢያ ቤተ ክርስቲያን በኩል የእግዚአብሔርን መንግሥት ለማስፋት ይሠራሉ። አልቪን ሳንደርስ የወርልድ ኢምፓክት ፕሬዝዳንት እና ሲ.ኢ.ኦ. መጋቢት 19፥ 2016 ዓ.ም.

የቤተ ክርስቲያን ተከላ ዳይሬክተር መልእክት የአጽናፈ ዓለሙ ገዥ ትርክት የሁለት መንግሥታት ግጭት እውነታ ነው። የእግዚአብሔር መንግሥት በአሸናፊው፥ በናዝሬቱ ኢየሱስ አማካይነት ድል አድርጓል። በትሥጕቱ፣ በስቅለቱና በትንሣኤው አማካይነት ኢየሱስ

Made with FlippingBook - Share PDF online