Foundations for Christian Mission, Amharic Student Workbook
2 0 2 /
የ ክ ር ስ ቲ ያ ን ሚ ሽ ን መ ሰ ረ ቶ ች
አ ባ ሪ 2 እናምናለን: የኒቂያ የሃይማኖት መግለጫ (የጋራ ሜትር *) ቄስ ዶ / ር ዶን ኤል ዴቪስ ፣ 2007
ማስታወሻ: ይህ መዝሙር ከእንግሊዝኛው የኒቂያ የሃይማኖት መግለጫ የተወሰደ የመዝሙር ግጥም ሲሆን (8.6.8.6.) በሆነ የጋራ ሜትር ተቀናብሯል፤ ስለዚህ እንደ O, for a Thousand Tongues to Sing; Alas, and Did My Savior Bleed?; Amazing Grace; All Hail the Power of Jesus’ Name; There Is a Fountain; Joy to the World ከመሳሰሉት መዝሙሮች ጋር በተመሳሳይ ሜትር ሊዘመር ይችላል።
ሁሉን ቻይ እግዚአብሔር አብ ሁሉን ይገዛል ፣ የምድርና የሰማይ ፈጣሪ ፡፡ አዎን ፣ የሚታየውና የማይታየው ሁሉ በእርሱ ተፈጥረዋል፣ ተሰጥተዋል!
አንድ ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስን እንጠብቃለን ፣ የእግዚአብሔር አንድያ ልጅ ፣ የተወለደ፣ ያልተፈጠረ፣ እርሱ እና ጌታችን አንድ ናቸው!
ከአብ የተወለደ ፣ አንድ የሆነ ፣ በማንነቱ አምላክ እና ብርሃን; ሁሉ በእርሱ በእግዚአብሔር የተደረገ ፣ በእርሱ ሕይወት ተሰጥቷል።
ስለ እኛ ለማዳን ከሰማይ ወደ ምድር የወረደ በመንፈስ ቅዱስ ኃይልና ከድንግል ማርያም በሆነ ልደት ሥጋ የለበሰ
በጴንጤናዊው በጲላጦስም እጅ መከራን በተቀበለ፥ በተሰቀለ በሞተ ፣ በተቀበረ በሦስተኛው ቀን ከሙታን በተነሳ
በቅዱሳት መጻሕፍት መሠረት ወደ ሰማይ ባረገ ፣ በአባቱም ቀኝ በተቀመጠ ፡፡
በሕያዋንና በሙታን ላይ ለሚፈርድ ፣ እንደገና በክብር የሚመለስ ለመንግሥቱም መጨረሻ የለውም ፡፡
እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስን እናመልካለን ፣ በጌታ እና ሕይወት በሚሰጥ ፣ ከአብ እና ከወልድ ጋር የሚመለክና የሚከበር ፣ በነቢያት የተናገረ ፡፡
በአንዲት እውነተኛዋ ቤተክርስቲያን እናምናለን ፤ ለሁልጊዜውም የእግዚአብሔር ህዝቦች ካቶሊካዊት እና በሐዋርያት መስመር ላይ የተመሰረተች
ለኃጢአት ይቅርታ አንዲትን ጥምቀት እንቀበላለን ፣ የሙታንንም ትንሳኤ እንጠብቃለን - ሙታን እንደገና ህያው እንደሚሆኑ
የማያልቁትን ቀናት እንጠባበቃለን - የሚመጣውም የዘላለም ሕይወት የክርስቶስ ታላቅ ግዛት ወደ ምድር ሲመጣ እና የእግዚአብሔር ፈቃድ ሲፈጸም!
Made with FlippingBook - Online catalogs