Foundations for Christian Mission, Amharic Student Workbook

2 0 2 /

የ ክ ር ስ ቲ ያ ን ሚ ሽ ን መ ሰ ረ ቶ ች

አ ባ ሪ 2 እናምናለን: የኒቂያ የሃይማኖት መግለጫ (የጋራ ሜትር *) ቄስ ዶ / ር ዶን ኤል ዴቪስ ፣ 2007

ማስታወሻ: ይህ መዝሙር ከእንግሊዝኛው የኒቂያ የሃይማኖት መግለጫ የተወሰደ የመዝሙር ግጥም ሲሆን (8.6.8.6.) በሆነ የጋራ ሜትር ተቀናብሯል፤ ስለዚህ እንደ O, for a Thousand Tongues to Sing; Alas, and Did My Savior Bleed?; Amazing Grace; All Hail the Power of Jesus’ Name; There Is a Fountain; Joy to the World ከመሳሰሉት መዝሙሮች ጋር በተመሳሳይ ሜትር ሊዘመር ይችላል።

ሁሉን ቻይ እግዚአብሔር አብ ሁሉን ይገዛል ፣ የምድርና የሰማይ ፈጣሪ ፡፡ አዎን ፣ የሚታየውና የማይታየው ሁሉ በእርሱ ተፈጥረዋል፣ ተሰጥተዋል!

አንድ ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስን እንጠብቃለን ፣ የእግዚአብሔር አንድያ ልጅ ፣ የተወለደ፣ ያልተፈጠረ፣ እርሱ እና ጌታችን አንድ ናቸው!

ከአብ የተወለደ ፣ አንድ የሆነ ፣ በማንነቱ አምላክ እና ብርሃን; ሁሉ በእርሱ በእግዚአብሔር የተደረገ ፣ በእርሱ ሕይወት ተሰጥቷል።

ስለ እኛ ለማዳን ከሰማይ ወደ ምድር የወረደ በመንፈስ ቅዱስ ኃይልና ከድንግል ማርያም በሆነ ልደት ሥጋ የለበሰ

በጴንጤናዊው በጲላጦስም እጅ መከራን በተቀበለ፥ በተሰቀለ በሞተ ፣ በተቀበረ በሦስተኛው ቀን ከሙታን በተነሳ

በቅዱሳት መጻሕፍት መሠረት ወደ ሰማይ ባረገ ፣ በአባቱም ቀኝ በተቀመጠ ፡፡

በሕያዋንና በሙታን ላይ ለሚፈርድ ፣ እንደገና በክብር የሚመለስ ለመንግሥቱም መጨረሻ የለውም ፡፡

እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስን እናመልካለን ፣ በጌታ እና ሕይወት በሚሰጥ ፣ ከአብ እና ከወልድ ጋር የሚመለክና የሚከበር ፣ በነቢያት የተናገረ ፡፡

በአንዲት እውነተኛዋ ቤተክርስቲያን እናምናለን ፤ ለሁልጊዜውም የእግዚአብሔር ህዝቦች ካቶሊካዊት እና በሐዋርያት መስመር ላይ የተመሰረተች

ለኃጢአት ይቅርታ አንዲትን ጥምቀት እንቀበላለን ፣ የሙታንንም ትንሳኤ እንጠብቃለን - ሙታን እንደገና ህያው እንደሚሆኑ

የማያልቁትን ቀናት እንጠባበቃለን - የሚመጣውም የዘላለም ሕይወት የክርስቶስ ታላቅ ግዛት ወደ ምድር ሲመጣ እና የእግዚአብሔር ፈቃድ ሲፈጸም!

Made with FlippingBook - Online catalogs