God the Father, Amharic Mentor Guide
/ 4 1
እግዚአብሔር አብ
እግዚአብሔር እንደ ፈጣሪ የእግዚአብሔር መግቦት
ትምህርት 2
ገጽ 259 1
የትምህርቱ ዓላማዎች
ኃያል በሆነው በጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ስም ሰላም ለአንተ ይሁን! የዚህን ሞጁል (ትምህርት) መጽሐፍ ካነበብክ፣ ካጠናህ፣ ውይይት ካደረግህና ወደ ተግባር ከቀየርክ በኋላ የሚከተሉትን ማድረግ ትችላለህ:- • የእግዚአብሔር የበላይ ስልጣን እና መግቦት በፍጥረት እና በታሪክ ሁሉ ላይ እንዴት እንደሚታይ ማብራራት ትችላለህ። • “መግቦት” ማለት “እግዚአብሔር ለራሱና ለፍጥረታቱ ለበጎ ያለውን ዓላማውን ለመፈጸም ሁሉም ነገሮች በእሱ ፍላጎት የተያዙበትን ሉዓላዊ ፈቃዱን በአጽናፈ ዓለም ውስጥ ይሠራል” ማለት እንደሆነ ማሳየት ትችላለህ። • እግዚአብሔር አብ በልጁ በኢየሱስ ክርስቶስ በኩል ሉዓላዊ፣ የሁሉም ነገር ምንጭ እና የሁሉ አኗሪ እንደሆነ ለማሳየት ቅዱሳት መጻሕፍትን መጠቀም ትችላለህ። እርሱ ክብሩን ሁሉ ይወስድ ዘንድ ሁሉም ነገር ከእርሱ ፈቃድ ጋር ለመስማማት እንደተዘጋጀ ማሳየት ትችላለህ። • የእግዚአብሔር ልዩ የመግቦት ሥራ በእርሱ ሁለንተናዊ ጥበቃ እና አገዛዝ እንዴት እንደሚገለጥ ማሳየት ትችላለህ። • ከዘመናዊው ፍልስፍና እና ሃይማኖት ጋር ከተያያዙት ስህተቶች ውስጥ ምን ያህሉ እግዚአብሔር በፍጥረት እና በታሪክ ላይ ያለውን መግቦት ካለመረዳት እንደመጡ ግልጽ ማድረግ ትችላለህ። • በክርስቶስ ዳግም ምጽአት ፍጥረትን ወደነበረበት ለመመለስ እግዚአብሔር ካለው ፍላጎት አንጻር ስለ እግዚአብሔር የጥበቃ እና የአገዛዝ ቁልፍ አካላት ያለህን ግንዛቤ ማሳየት ትችላለህ። • መግቦተ እግዚአብሔር እንደ ፓንቴይዝም፣ ዴኢዝም፣ ፋታሊዝም እና አጋጣሚ ላሉ አንዳንድ ዘመናዊ የፍልስፍና እና የነገረ-መለኮት ስህተቶችን እንዴት እንደሚፈታ በአጭሩ ማብራራት ትችላለህ። በእውነቱ አንድ ዓይነት 1 ጢሞ. 6፡13-16 ሁሉን በሕይወት በሚጠብቅ በእግዚአብሔር ፊት፥ በጴንጤናዊውም በጲላጦስ ዘንድ መልካሙን መታመን በመሰከረ በክርስቶስ ኢየሱስ ፊት አዝሃለሁ፤ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እስኪገለጥ ድረስ ያለ እድፍና ያለ ነቀፋ ሆነህ ትእዛዙን ጠብቅ፤ ያንም መገለጡን በራሱ ጊዜ ብፁዕና ብቻውን የሆነ ገዥ፥ የነገሥታት ንጉሥና የጌቶች ጌታ፥ ያሳያል። እርሱ ብቻ የማይሞት ነው፤ ማንም
2
ጥሞና
ገጽ 260 2
Made with FlippingBook - Online magazine maker