God the Father, Amharic Mentor Guide

5 8 /

እግዚአብሔር አብ

(4) ነፋሱን ዘርተው አውሎ ነፋሱን አጨዱ፣ ሆሴ. 8.7.

(5) ጽድቅን ዘርተህ ዋጋውን በአይነት ታጭዳለህ፣ ሆ. 10.12.

(6) ሰው ሁሉ እንደ ሥራው ይቀበላል፣ ሮሜ. 2.6-10.

III. ሁሉን ቻይ የሆነው እግዚአብሔር አብ እንደ ሁሉም ነገር ጠባቂ እና ገዥ በተሰኘው ትምህርት ውስጥ ያሉ ቁልፍ አስተምህሮዎች

የእግዚአብሔር የመግቦት አስተምህሮ ዘመናዊ የፍልስፍና እና የስነ-መለኮት ስህተቶችን ውድቅ ያደርጋል።

2

ሀ. ስህተት አንድ፡ እግዚአብሔር የፍጥረት አካል ነው ማንነቱም ከፍጡር የተለየ አይደለም።

1. እርሱ ከአጽናፈ አለም ማንነት የተለየ ነው (የፍጡራን ሥርዓት አካል አይደለም)

2. እርሱ ከሌሎች ፍጥረታት ሁሉ ማንነትና ስብዕና የተለየ ነው (ራሱን ለሰው ልጆች ይገልጣል፤ የውስጣዊ ማንነታቸው ወይም የአፈጣጠራቸው አካል አይደለም)።

3. እግዚአብሔር ካለመኖር ex nihilo (“ከምንም”) አጽናፈ አለሙን የፈጠረ ነው።

ሀ. ይህ ፓኔንቲዝምን ውድቅ ያደርጋል (እግዚአብሔር ከቁሳዊ ነገሮች ጋር በተወሰነ መሰረታዊ መንገድ የተገናኘ እና አብሮ የሚኖር መሆኑን)።

ለ. ይህ ፓንቴዝምን ውድቅ ያደርጋል (እግዚአብሔር በቀጥታ ከአጽናፈ ዓለሙ ጉዳይ ጋር የተያያዘ ነው ወይም ይመነጫል የሚለውን)።

ለ. ስህተት ሁለት፡- እግዚአብሔር አሁን ካለው የአጽናፈ አለም አሠራር ፈጽሞ የተለየ ነው።

1. እግዚአብሔር ዓለምን ፈጥሮ በራሱ (እንደ ማሽን) እንዲሠራ አልተወውም።

Made with FlippingBook - Online magazine maker