God the Father, Amharic Mentor Guide

/ 9 7

እግዚአብሔር አብ

* “ሥላሴ” የሚለው ቃል ራሱ በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ሳይኖር ሥነ መለኮት ይህን የእምነት “አስፈላጊ ትምህርት” እንዲሆን የሚያደርገው እንዴት ነው? * አንድ ሰው ስለ እግዚአብሔር የይሖዋ ምስክሮች እንደሚያምኑት (እግዚአብሔር አብ ብቻ አምላክ ነው፤ ኢየሱስ በእግዚአብሔር የተፈጠረ ሁለተኛው ታላቅ ፍጡር ነው እና መንፈስ ቅዱስ ደግሞ ለአገልግሎት የእግዚአብሔር ኃይል ነው) ብሎ ቢያምን ይህ መጽሐፍ ቅዱሳዊ እንደሆነ ይቆጠራልን? ለምን? * የእግዚአብሔርን ታላቅነት በምታደርገው ነገር ሁሉ ማለትም በአምልኮህ፣ በምግባርህና በባሕርይህ እንዲሁም በአገልግሎትህ ላይ ተጽዕኖ እንደሚያሳድር እንዴት ትረዳለህ? ይህንን ከፍ ያለ እውነት ለእግዚአብሔር ወደሆነ ፍጹም የአኗኗር ዘይቤ እንዴት ትተረጉመዋለህ? * ብዙዎች እግዚአብሔርን የሚመለከቱት ፍላጎታቸውን ለማሟላት እንደሚፈልግ እንጂ እንደ ሥላሴ እና የአጽናፈ ዓለማት ሉዓላዊ አምላክ አይደለም። እግዚአብሔር ለኔ የሚኖር አምላክ ነው ከሚለው ሁሉ ነገሮች ለእግዚአብሔር ነው የሚኖሩት ወደሚለው አመለካከት እንዴት መቀየር ይቻላል? * በማደግ ላይ ያሉ አማኞች የእግዚአብሔርን ማንነት፣ ባሕርያትና ስም በተመለከተ የእግዚአብሔርን ቃል “ጥልቅ እውነቶች” እንዲማሩ ለመርዳት ምን ተግባራዊ መንገዶች አሉ? * የእግዚአብሔር ታላቅነት ባህሪያት (ማለትም፣ መንፈሳዊነቱ፣ ህይወቱ፣ ስብዕናው፣ ወሰን የለሽነቱ እና ቋሚነቱ) ከአስተሳሰባችን እጅግ የመጠቀ መሆኑን ይናገራሉ። በኢየሱስ ክርስቶስ በኩል ያለን እምነት አብን ለእኛ ይበልጥ ቅርብ የሚያደርገው እንዴት ነው (ዮሐንስ 1.18፤ ዮሐንስ 14.7-9)? “አስፈላጊ አይመስልም” ስለ እግዚአብሔር ባህሪያት ላይ በሚደረግ የመጋቢዎች የሳምንት አጋማሽ የመጽሐፍ ቅዱስ ተከታታይ ጥናት ላይ አንዲት የተራበች አዲስ አማኝ ወጣት እጇን አውጥታ ስለ ጥናቱ አስተያየት ሰጠች። “ፓስተር” ብላ ይቅርታ ጠይቃ፣ “ይህ በሴሚናሪ ትምህርት ውስጥ ጠቃሚ ሊሆን እንደሚችል አውቃለሁ፣ ግን በእውነቱ፣ ስለ እግዚአብሔር እነዚህን ሁሉ አስቂኝ ቃላቶች እና ነገሮች ለምን ማጥናት እንዳለብን ለመረዳት እየተቸገርኩ ነው። ለምን ክርስቲያኖች ከረጅም ጊዜ በፊት ስለ አምላክ ተፈጥሮ ያመኑትን መረዳት እንዳለብን ወይም እንደ ousios ወይም homousia ያሉትን ማንኛውንም ማንኛውንም ቃል ማወቅ ለምን እንደሚያስፈልገን አልገባኝም። እኔ ማወቅ የምፈልገው ስለ ኢየሱስ እንጂ ስለ ዶክትሪን የማወቅ ብዙም ፍላጎቱ የለኝም። እስኪ በፈጠራችሁ እኔ እንደ አዲስ ክርስቲያን ስለ እነዚህ ሁሉ ነገሮች ለምን ትኩረት መስጠት እንዳለብኝ ንገሩኝ - ለእኔ ብዙም አስፈላጊ አይመስለኝም፣ እኔ ከማደርገው ነገር ጋርም ምንም ግንኙነት የለውም። እንደ መጋቢ፣ ይህች በክርስቶስ የተወደደች እህት ለምታነሳው እውነተኛ ጥያቄ ምን ምላሽ ትሰጣለህ?

3

ጥናቶች

1

ገጽ 270  6

Made with FlippingBook - Online magazine maker