Bible Interpretation, Amharic Mentor Guide

/ 9 7

የመጽሐፍ ቅዱስ ሥነ-አፈታት

ቅዱስ ትርጓሜዎች የእግዚአብሔርን ቃል ለህይወት ለውጥ አላማ እንጂ ለአእምሮ መረጃ ለመስጠት አይደሉም። ³ የሶስት-ደረጃ ሞዴል የመጽሐፍ ቅዱስ ትርጓሜ ውጤታማ ዘዴ ሲሆን በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ የሚገኙ የተለያዩ ቁሳቁሶችን (ቃላትን፣ አንቀጾችን፣ ምዕራፎችን፣ መጻሕፍትንና ክፍሎችን) በመጠቀም ውጤታማ በሆነ መልኩ ጥቅም ላይ ሊውል ይችላል። ³ ሁሉም የእግዚአብሔር ቃል ጥናት የሚጀምረው እርሱ ብቻውን የቅዱሳት መጻሕፍት ባለቤት እና ለእኛ ዛሬ ለሕይወታችን ያለውን ትርጉምና ፋይዳ ሊያስተምረን በቂ ለሆነው ለመንፈስ ቅዱስ በመገዛት ነው። በመንፈስ ቅዱስ ላይ ያለን መተማመን የቃሉን ጥናት በትጋት እንድናደር እንጂ የቃሉ ምትክ እንዲሆን አይደለም። ³ የሶስት ደረጃ ሞዴልን ለመጠቀም የመጀመሪያው እርምጃ የጽሑፉን ዝርዝር ሁኔታ፣ የመጽሐፉን አመጣጥ፣ ደራሲውን እና ተደራሲውን፣ የተፃፈበትን ዓላማ፣ እንዲሁም በተለያዩ ትርጉሞች የሚሰጠውን ትርጉም አተረጓጎም መመልከት ነው። ³ የጽሑፉን ወይም ምንባቡን አጠቃላይ መርሆች ማግኘት የሶስት-ደረጃ ሞዴል ሁለተኛ ደረጃ ነው፣ እና በጽሁፉ ውስጥ የተካተቱትን ማዕከላዊ መልዕክቶችን፣ እውነቶችን፣ ትዕዛዞችን ወይም ትምህርቶችን ማግኘትን ያካትታል። ይህ ደረጃ ጽሑፉ በዋናው ዓውድ ውስጥ ምን ማለት እንደሆነና አሁን በእኛ ሕይወት ውስጥ ወደሚኖረው ትርጉም መሄድን ያካትታል። እነዚህ መሠረታዊ ሥርዓቶች በመላው ቅዱሳን መጻሕፍት ውስጥ ካሉት ትምህርቶች ጋር ተነፃጽረው ለተጨማሪ ጥናትና ተግባራዊነት በግልጽ መቀመጥ አለባቸው። ³ ዝርዝሮቹን ከተመለከትን እና መርሆችን ካወጣን በኋላ፣ ወደ ሶስት ደረጃ ሞዴል ሦስተኛው ደረጃ እንሄዳለን፣ እርሱም በመንፈስ ቅዱስ ኃይል መንፈሳዊ መርሆችን በህይወታችን ውስጥ ተግባራዊ ማድረግ ነው። ተግባር መንፈስ እንደመራን ለእግዚአብሔር እውነት ልብን የማፍሰስ መገለጫ ነው። ለሕይወታችን የእግዚአብሔርን ፈቃድ ለመታዘዝ ማስተዋልን እና ዝግጁነትን ይጠይቃል። ³ ሁሉም የመጽሐፍ ቅዱስ ትርጉሞች የተሰጡት በክርስቶስ ደቀ መዝሙርነታችንን ለማጠናከር ሲሆን በቅዱሳት መጻሕፍት ውስጥ አጽንዖት በተሰጣቸው የጋራ ጭብጦች ላይ ልዩነት ያሳያሉ። ለእግዚአብሔር እና ለባልንጀራችን ያለንን ፍቅር እንዲሁም ነፃነታችንን ሌሎችን ለማነጽና እግዚአብሔርን ለማክበር መጠቀማችን በብሉይም ሆነ በአዲስ ኪዳን የመጽሐፍ ቅዱስ የሥነ ምግባር መርሆዎች ዋና ዋና ክፍሎች ናቸው።

2

Made with FlippingBook flipbook maker