Bible Interpretation, Amharic Student Workbook
/ 2 9
የመጽሐፍ ቅዱስ ሥነ-አፈታት
3. ያለማቋረጥ ለእግዚአብሔር ቃል በመታዘዝ ከሕፃንነት ወደ ልጅነት ብሎም ወደ ጉልምስና እናድጋለን።
ሀ. 1 ጴጥ. 2.2
ለ. ዕብ. 5.12-6.1
ማጠቃለያ
1
» ቅዱሳት መጻሕፍትን በትክክል ለመተርጎም ልባችንን፣ አእምሯችንን እና ፈቃዳችንን ለሕያው እግዚአብሔርን ዘላለማዊ ቃል ማዘጋጀት አለብን። » እንደ መለኮታዊ እና ሰዋዊ መጽሐፍ፣ የእግዚአብሔርን ቃል ለመረዳት በመንፈስ ቅዱስ ስጦታዎች ላይ መደገፍ እና ቃሉን ከመተግበራችን በፊት ህይወታችንን እንዲለውጥ ለመፍቀድ ዝግጁ መሆን አለብን።
እባክህ በነዚህና በሌሎችም በዚህ ቪዲዮ ላይ ለተነሱ ጥያቄዎች በቂ ጊዜ ወስደህ ምላሽ ለመስጠት ሞክር፡፡ የመጽሐፍ ቅዱስ ስነ አፈታትን ርእሰ ጉዳይ የከበሩ የቅዱሳት መጻሕፍት ግንዛቤዎችን ብቻ የሚያስገኙ ሕጎችና ዘዴዎች ጥርቅም ብቻ አድርገን ልንመለከተው አይገባም። ይልቁንም፣ አጠቃላይ ርዕሰ ጉዳዩ መንፈሳዊ ጉዳይ ነው፤ ትክክለኛ የመጽሐፍ ቅዱስ ትርጓሜም ሁል ጊዜ መንፈሳዊ ዝግጅትን ይጠይቃል፣ ቅዱሳት መጻሕፍትን ለመረዳት ብቻ ሳይሆን በሁሉም የሕይወታችን ዘርፎች ለማሟላት የሚፈልግ መሠረት ነው። ከዚህ ቀጥሎ የቀረቡትን የመጀመርያውን ሴግመንት ቁልፍ ጽንሰ ሐሳቦች ማጠቃለያ ጥያቄዎች ከእነዚህ እውነቶች አንጻር ተመልከታቸው፤ መልሶችህን በቅዱሳት መጻሕፍት አስደግፍ። 1. የስነ አፈታት ሳይንስ ምንድነው፣ ስለምንስ ጉዳይ ያጠናል? የመጽሐፍ ቅዱስ ስነ አፈታት ጥናት የሚያመጣው ልዩ ተግዳሮት እና ግብ ምንድን ነው? 2. መጽሐፍ ቅዱስ እንደ መለኮታዊም ሆነ እንደ ሰብዓዊ መጽሐፍ ተደርጎ መወሰድ አለበት ሲባል ምን ማለት ነው? መጽሐፍ ቅዱስ ሰዋዊ መጽሐፍ ነው ብሎ መናገር መጽሐፍ ቅዱስ ከእግዚአብሔር የመነጨ ነው የሚለውን ሐሳብ ያቃልለዋል? አብራራ። 3. የመጽሐፍ ቅዱስ ትርጓሜ ዓላማ ምንድን ነው? በሌላ አነጋገር መጽሐፍ ቅዱስን ስናጠና ምን ለማድረግ መጣር አለብን? ‘የእውነትን ቃል በቅንነት መያዝ’ ሲባል ምን ማለት ነው? (2 ጢሞ. 2.15)?
መሸጋገሪያ 1
የተማሪ ጥያቄዎች እና ምላሾች
Made with FlippingBook - Online Brochure Maker