Bible Interpretation, Amharic Student Workbook

/ 3 1

የመጽሐፍ ቅዱስ ሥነ-አፈታት

የመጽሐፍ ቅዱስ እስትንፋሰ እግዚአብሔር፡ የመጽሐፍ ቅዱስ አመጣጥ እና ሥልጣን ክፍል 2፡ መጽሐፍ ቅዱሳዊ እስትንፋሰ እግዚአብሔር እና ዘመናዊ መጽሐፍ ቅዱሳዊ ትንተና

ቄስ ዶክተር ዶን ኤል ዴቪስ

መጽሐፍ ቅዱስ ራሱ እንደሚናገረው መጽሐፍ ቅዱስ በእግዚአብሔር መንፈስ አነሳሽነት የተጻፈ ሲሆን የእግዚአብሔርና የሰዎች ባሕርይም የመጽሐፉ ምንጭ እንደሆነና ሕያው የሆነው አምላክ ቃል መሆኑን ያረጋግጣል። ክርስቲያኖች የእግዚአብሔር ቃል በእግዚአብሔር መንፈስ አነሳሽነት የተጻፈ ስለሆነ፣ በመጀመሪያዎቹ ቅጂዎች ውስጥ ምንም ዓይነት ስህተት እንደሌለበት፣ በዚህም ምክንያት በእግዚአብሔር ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ምን ማመንና ምን ማድረግ እንዳለብን የሚወስን ፍጹም ሥልጣን እንዳለው ያምናሉ። በዘመናችን ያሉ የመጽሐፍ ቅዱስ ተንታኞች የመጽሐፍ ቅዱስን አመጣጥ በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ከተጠቀሱት የመጀመሪያዎቹ ክንውኖች በመነሳት በቅዱሳት መጻሕፍት ውስጥ ከተመዘገቡት ክንውኖች ጋር ለማዛመድ ይጥራሉ። እነዚህ ዋና ዋና ክፍሎች ቅርጽ፣ ምንጭ፣ የስነ ቋንቋ፣ የጽሑፍ፣ ሥነ-ጽሑፋዊ ፣ ቀኖናዊ እና ታሪካዊ ትንተናዎችን እንዲሁም የትርጉም ጥናቶችን ያካትታሉ። በዛሬው ጊዜ ያሉ ብዙ ምሁራን የሚይዙት አቋም ምንም ይሁን ምን ቅዱሳት መጻሕፍት በእርግጥ የሕያውና ለዘላለማዊው አምላክ የእግዚአብሔር ቃል እንደሆነ እርግጠኞች መሆን እንችላለን። የዚህ መጽሐፍ ቅዱሳዊ እስትንፋሰ እግዚአብሔር እና ዘመናዊ መጽሐፍ ቅዱሳዊ ትንተና የተሰኘ ሴግመንት ዓላማ የሚከተሉትን እንድትገነዘብ ማስቻል ነው፦ • ቅዱሳት መጻሕፍት በግልጽ እና በድፍረት መጽሐፍ ቅዱስ በመንፈስ ቅዱስ ኃይል እና አሠራር በእግዚአብሔር መንፈስ መሪነት “እስትንፋሰ እግዚአብሔር” እንደሆነ ይናገራሉ። መጽሐፍ ቅዱስ በሰዎች ደራሲነት እና በመለኮታዊ አነሳሽነት የተጻፈ መጽሐፍ ነው፣ ነገር ግን የትኛውም ቅዱስ መጽሐፍ በግለሰብ ፈቃድ የተተረጎመ አይደለም፣ ነገር ግን ደራሲዎቹ በመንፈስ ቅዱስ “ተነድተዋል”። • ቅዱሳት ጽሑፎችን የጻፉት ሰዎች በመንፈስ ቅዱስ ተመርተው የተጻፉ መሆናቸውን የሚያረጋግጡት አምስት ዋና ዋና የመንፈስ አነሳሽነት ንድፈ ሐሳቦች ናቸው። እነዚህም ሜካኒካል ወይም ዲክቴሽን ቲዎሪ፣ ኢንቱይሽን ወይም ናቹራል ቲዎሪ፣ የኢሉሚኔሽን ቲዎሪ፣ ዘ ዲግሪስ ኦፍ ኢንስፓየሬሽን ቲዎሪ እና ቨርባል/ፕሌነሪ ቲዎሪ ይገኙበታል። ቨርባል/ ፕሌነሪ ቲዎሪ፣ ጸሐፊው የመረጣቸውን ቃላት ጨምሮ የቅዱሳት መጻሕፍቱ ሙሉ ጽሑፍ የእግዚአብሔር መሪነትና ምርጫ ውጤት ነው የሚል ነው። • በዘመናችን ያሉ የመጽሐፍ ቅዱስ ተንታኞች የመጽሐፍ ቅዱስን አመጣጥ በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ከተጠቀሱት የመጀመሪያዎቹ ክስተቶች በመነሳት በመጽሐፍ ቅዱስ ቅጂዎች ውስጥ ከተመዘገቡት ክስተቶች ጋር ለማገናኘት ይጥራሉ። ከቁጥጥር ክስተት ጀምሮ የእግዚአብሔርን መልእክት ከድርጊቱ ክዋኔ አንስቶ ዛሬ እስካለን የቅዱሳት መጻሕፍት ትርጉም ድረስ ለመከታተል ይሞክራል ።

የሴግመንት 2 ማጠቃለያ [የጎን ማስታወሻ]

1

Made with FlippingBook - Online Brochure Maker