Bible Interpretation, Amharic Student Workbook

3 4 /

የመጽሐፍ ቅዱስ ሥነ-አፈታት

2. ቅዱሳት መጻሕፍት በእግዚአብሔር መንፈስ አነሳሽነት የተጻፉ በመሆናቸው፣ በቤተክርስቲያን ውስጥ ማመንና ማድረግ ስላሉብን ነገሮች ቅዱሳት መጻሕፍት ብቻ የመጨረሻው እና ፍፁም ባለሥልጣን መሆናቸውን እናረጋግጣለን።

II. የእስትንፋሰ እግዚአብሔር ጽንሰ-ሀሳቦች፡ መንፈስ ቅዱስ እንዴት ደራሲ ሰዎችን በትክክል መራ? እነዚህ ንድፈ ሐሳቦች ጌታ፣ መንፈስ እንዴት ደራሲዎቹን እንዳነሳሳቸው፣ ያመጡት ውጤት “በእግዚአብሔር አነሳሽነት” የመጣ ነው እንዴት ሊባል ይችላል የሚለውን ጥያቄ ለመመለስ ይፈልጋሉ።

በዚህ ክፍል ውስጥ ያለው የክርክር አወቃቀር ከ H. Wayne House, “Theories of Inspiration.” Charts of Christian Theology. Grand Rapids: Zondervan, 1992 የተወሰደ ነው።

1

ሀ. መካኒካል ወይም ዲክቴሽን ቲዎሪ፡ ተሳትፎ አልባ የሰው ደራሲነት

1. ደራሲው ሰው በእግዚአብሔር እጅ ውስጥ ተሳትፎ አልባ መሳሪያ ነበር።

2. ፀሐፊው እያንዳንዱን ቃል እግዚአብሔር እንደተናገረው ጻፈ (በቃል ዘገባ፣ እንደ ጸሐፊ)።

3. ይህ አጻጻፍ ቅዱሳት መጻሕፍትን ከስህተት ይጠብቃል።

4. ለሜካኒካል ወይም ለዲክቴሽን ቲዎሪ ምላሽ

ሀ. ይህ እውነት እንዳይሆ የመጽሐፍ ቅዱስ መጻሕፍት በጣም ብዙ የአጻጻፍ ስልት፣ የቋንቋ እና የአገላለጽ ስልት ልዩነቶችን ያሳያሉ።

ለ. ታዲያ ለምን እግዚአብሔር መጽሐፉን ሙሉውን አልሰጠንም?

Made with FlippingBook - Online Brochure Maker