Church PLANT Manual, Amharic Edition

ክፍል 1፥ ዝግጅት • 19

ስለሚማሩት፣ ወይም ስለሚጫወቱት ነገር ግልጽ ራእይ አላቸው። ግልጽ ዐላማና ራእይ ከሌለ ሰዎች የትኛው ጥረታቸው አስቸጋሪና አዳጋች ይሆናል። II. የባለቤትነት ስሜት አካል የተሠራው ከብዙ ብልቶች እንጂ ከአንድ ብልት አይደለም። እግር፣ “እኔ እጅ ስላልሆንሁ የአካል ክፍል አይደለሁም” ቢል ይህን በማለቱ የአካል ክፍል መሆኑ ይቀራልን? ጆሮም፣ “እኔ ዐይን ስላልሆንሁ የአካል ክፍል አይደለሁም” ቢል ይህን በማለቱ የአካል ክፍል መሆኑ ይቀራልን? አካል በሙሉ ዐይን ቢሆን ኖሮ፣ መስማት ከየት ይገኝ ነበር? አካል በሙሉ ጆሮ ቢሆን ኖሮ፣ ማሽተት ከየት ይገኝ ነበር? ነገር ግን እግዚአብሔር እንደ ወደደ እያንዳንዱን በየቦታው መድቧል። ሁሉም አንድ ብልት ቢሆን ኖሮ አካል ከየት ይገኝ ነበር? እንግዲህ ብልቶች ብዙ ናቸው፣ አካል ግን አንድ ነው (1 ቆሮንቶስ 12፥14-17)። ይናገራል። አስቂኝ በሚመስል መልኩ እግርና እጅ የአካሉ ክፍል እንዳልሆኑ ይናገራሉ። በተመሳሳይ መልኩ የቤተ ክርስቲያን አባላት ወይም የቡድናችሁ አባላት፣ “የዚህ ቡድን አባል አይደለሁም” ሊሉ ይችላሉ። ብዙውን ጊዜ አንዳንድ የቡድናችሁ አባላት የሚሰማቸው ልክ እንዲህ ነው። ባለማወቅም ይሁን የቡድናችሁ አባላት በቡድኑ ውስጥ የባለቤትነት ስሜት የማይሰማቸው ከሆነ መለያየት ሊከሠት ይችላል። III.ለተለያዩ ስጦታዎች ዋጋ መስጠት 1ቆሮንቶስ 12፥11-27፤ ኤፌሶን 4፥11-16፤ 1ጴጥሮስ 4፥9-11፤ እና ሮሜ 12፥3-8 እነዚህ ጥቅሶች ሁሉ ስለ ልዩ ልዩ ስጦታዎችና እነዚህ ስጦታዎች አካሉን ለማነጽ ምን ያህል አስፈላጊ እንደሆኑ ይናገራሉ። በተጨማሪም ለእነዚህ ስጦታዎች ዋጋ መስጠትና እያንዳንዱ ሰው ሁሉም የቡድኑ አባላት ሊጠቀሙ በሚችሉበት መንገድ ስጦታቸውን የመጠቀማቸውን አስፈላጊነት ይናገራሉ። እንዲሁም የቤተ ክርስቲያን ተከላ ቡድንም የተለያዩ ተሰጥዎችና ስጦታዎች ያስፈልጉታል። ከእናንተ ስለ 1 ቆሮንቶስ 12፥11-27 እና ስለ ቡድን እንዲሁም ባሕርያት ብዙ ነገር ማለት ይቻላል። በቍጥር 14-17 ጳውሎስ ስለ ባለቤትነት ስሜት

Made with FlippingBook - Share PDF online