Church PLANT Manual, Amharic Edition

22 • የቤተ ክርስቲያን ተከላ መምሪያ

ዳዊትን ከዮናታን፣ ኤልያስን ከኤልሳዕ፣ ጳውሎስን ከበርናባስ፣ ሲላስና ሌሎች ጋራ። ጌታችንና መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስም ዐሥራ ሁለት ደቀ መዛሙርትን ጠርቶ ነበር። እነዚህ ሁሉ በራሳቸው ብቻ ከሚያመጡት ተጸዕኖ ይልቅ በጋራ ታላቅ ተጽዕኖ መፍጠር ችለዋል። የጌታ ኢየሱስን ምሥራች ማወጅ እንደሚሻ የቤተ ክርስቲያን ተከላ ቡድን ምስክርነታችን ለዓለም የሚታወቀው ርስ በርስ ባለን መዋደድና የፍቅር ተግባር ነው። የአማኞች ማኅበረ ሰብ ለመመስረት መጀመሪያ የአማኞች ማኅበረ ሰብ ምን እንደሚመስል ማሳየት አለባችሁ። ይህ ዐዲስ ቡድን የቡድን ጓደኞቻችሁን ጨምሮ ሌሎችም በነጻነት የሚመላለሱበት ቡድን ሊሆን ይችላል። ዋናው ነገር ጌታ ከሰጣችሁ ቡድን ጋራ መሥራትና ጳውሎስ በተለያዩ ጒዞዎቹ እንዳደረገው መጀመር ነው። 2 “የቤተ ክርስቲያን ተከላ ቡድን፥ ቡድኑን እግዚአብሔር ሲመሠርተው ምን ሊያደርግ እንዳለ እንደሚያውቅ መረዳት ቀዳሚ መርሑ ነው። በቡድን በጋራ መሆን ጥሩ ሐሳብ ብቻ ሳይሆን የእግዚአብሔርም ሐሳብ ነው። አስቸጋሪ ጊዜያት ሲመጡ የቡድን መሪዎች ለቡድኑ አንድነት ይጋደላሉ፣ አንድነታቸውን ያረጋግጣሉ እንዲሁም ቡድናቸውን ይወድዳሉ። ይህ የእግዚአብሔር ሐሳብ እንደሆነ በልባቸው ያምናሉና።” 3

2 See “Paul’s Team Members: Companions, Laborers, and Fellow Workers” in The Timothy Conference Workbook , p. 129. 3 The Timothy Conference Workbook , p. 65.

Made with FlippingBook - Share PDF online