Church PLANT Manual, Amharic Edition

42 • የቤተ ክርስቲያን ተከላ መምሪያ

ከሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ጀምሮ እስከዛሬ ድረስ የቤተ ክርስቲያን ታሪክ ወንጌሉን ለማወጅ፣ ለመጠበቅ እና ለማስፋት ሕይወታቸውን የሰጡ ሰዎች ታሪክ ነው። አብያተ ክርስቲያን እና ቤተ ክርስቲያን ተካዮች በብዙ ነገሮች ተነሳስተው ይመራሉ። አንዳንዶች ለተሻለ ነገ፣ ለተሻሉ ባልጀሮች፣ ወይም ለተሻሉ አብያተ ክርስቲያናት ራእይ በመሰነቅ ይንቀሳቀሳሉ። እነዚህ ሁሉ መልካም ነገሮች ናቸው ነገር ግን በዋናነት የሚመራንና የሚያንቀሳቅሰን ወንጌል ሊሆን ይገባል። ስለዚህ የወንጌሉን መልእክት፣ ተልእኮ እና መንገዶች መረዳት በጣም አስፈላጊ ነው። ምን ማመን እንዳለብን፤ በዙሪያችን ያለውን ዓለም እንዴት ማየት እንዳለብንና ቤተ ክርስቲያንም ምን መሆን እንዳለባት የሚነግረን ወንጌል ነው። I. የወንጌሉ መልእክት • መጽሐፍ ቅዱስ አንድ ግልጽ ትዕይንትን ይተርካል ይህም የእግዚአብሔር ታሪክ ነው። ከዘፍጥረት እስከ ራእይ የእግዚአብሔር ፈቃድ ሰዎችን ለመቤዠት መሆኑ ግልጽ ነው። • በእግዚአብሔር ታሪክ ውስጥ ዋናው አሸናፊ ኢየሱስ ነው። • ሙሉው የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪክ ስለ ርሱ የሚናገር እንደሆነ ጌታችን ግልጽ አድርጓል. • ዐዲስ ኪዳን ስለተገለጠው ኢየሱስ ክርስቶስ ከሆነ ብሉይ ኪዳን ደግሞ ተሰውሮ ስለነበረው ኢየሱስ ክርስቶስ ነው የሚል አባባል አለ። 1 መጽሐፍ ቅዱሳችን ከመጀመሪያ እስከ መጨረሻው የሚተርከው ስለ ኢየሱስ ነው። • በመጽሐፍ ቅዱስ ታሪክ እና በመላው ዓለም በሚገኙ ልቦች ውስጥ ኢየሱስ ማእከላዊው፣ ዋናው፣ አቻ የሌለው የሆነው ለምንድን ነው? ምክንያቱም ከሰማይ ወደ ምድር የወረደ፣ ፍጹም ሰው ፍጹም አምላክ የሆነ፣ ፍጹም ሕይወት የኖረ፣ የስርየት ሞትን የሞተ፣ ኀጢአትን፣ ሰይጣንን፣ ጨለማንና ሞትን ድል ለማድረግ የተነሣ ርሱ ብቻ ነው። አዳም መኾን ያቃተውን ሁሉ፣ እስራኤል መሆን የተሳናትን ሁሉ፣ እኛ ሁላችን የወደቅንበትን ሁሉ ማድረግ የቻለው

1 Augustine’s statement from “Questions on the Heptateuch,” 2.73 in The Works of St. Augustine: Writings On The Old Testament .

Made with FlippingBook - Share PDF online