Church PLANT Manual, Amharic Edition
48 • የቤተ ክርስቲያን ተከላ መምሪያ
1. የዕውቀት ገጽታ፥ ይህ ባህሉ የሚያውቀውና እውነታና እውነት ብሎ የሚረዳቸው ነገሮች ናቸው። የዕውቀት ገጽታ 2. የስሜት ገጽታ፥ ይህ የስሜቶችና የስሜት መገለጫዎችን የሚመለከት ሲሆን ባህሉ የሚወድዳቸውንና የሚጠላቸውን ነገሮች የሚገልጽ ነው። 3. የምዘና ገጽታ፥ ይህ አንድ ባህል ዕሴቶቹን፣ የሰዎችን መስተጋብር ሥነ ምግባራዊና ኢ ሥነ ምግባራዊ (ትክክልና ስሕተት) በማለት የሚበይንበት ሥርዓት ነው። • በዋናነት ባህል ዕሴቶችን የተመለከተ ነው። ባህልን ለመረዳት ሰዎች ትልቅ ቦታ የሚሰጡት ነገር ምን እንደሆነና ለእነዚህ ነገሮች ከፍ ያለ ቦታ የሚሰጡት ለምን እንደሆነ መረዳትን ይጠይቃል። የሚወድዱት፣ የሚኖሩለት፡ የሚሞቱለት፣ ትልቅ ዋጋ የሚሰጡት ነገር ባህሉን የሚገልጽና ባህልን የሚፈጥር ነው። II. የባህል ልዩነቶችን መረዳት ባህልን ውጤታማ በሆነ መንገድ ለማሰስ ማወቅ ያለብን ባህል ምን ማለት እንደሆነ ብቻ ሳይሆን በተለያዩ ባህሎች መካከል ያለውንም ልዩነት መረዳት ይጠበቅብናል። • እግዚአብሔር ልዩ ልዩ አድርጎ ስለ ፈጠረን ልዩነቶች መልካም ናቸው፣ ሐዋርያት ሥራ 17። • በባህሎች (በሰዎች) መካከል ያለው ልዩነት ግልጽና ጉልህ ነው። • ባህላዊ ልዩነቶችን አሳንሶ መመልከት ወይም ችላ ማለት በወንጌል ላይ አሉታዊ ተጽዕኖ ሊያሳድር ይችላል።. III.ለየት ያለ ክርስቲያናዊ ባህል መመሥረት ነገር ግን ኢየሱስን ከምንም ነገር በላይ ከፍ አድርገው ለሚመለከቱ ክርስቲያኖች ባህል በሰዎች ስኬቶች የሚበየን አይደለም። ከዚህ ይልቅ “ኢየሱስ ጌታ ነው” በሚሉ ሦስት ቃላት ተገልጿል። ቤተ ክርስቲያን ለህልውናዋ የተለየ ምክንያት ያላት ስትሆን የተመሠረተችው፣ ህላዌዋን
Made with FlippingBook - Share PDF online