Fight the Good Fight of Faith, Amharic Edition
መግቢያ • 11
የሚያጋጥሟችሁን የተለያዩ ጉዳዮች የምትረዱበትን መረዳት ለማሻሻል እንድትችሉ መንፈስ ቅዱስ እንዲለውጣችህ ፍቀዱ።
ማገናኘት ይህ ክፍል በክፍሉ ውስጥ የተማረችኋቸውን እውነታዎች በተግባር መተግበራቸውን (“በተግባር ላይ መዋሉ”) እና ተጨባጭ መሆኑ ላይ ያተኩራል። በመሆኑም እናንተም የተማራችሁትን ትምህርት በአስተሳሰባችህ በንግግራቸሁ በተግባራችሁ እና ከሌሎች ጋር በሚኖራቸሁ ግንኙነት ውስጥ ሁለ የሚዛመዱበትንና የሚገናኙበትን መንገዶች ሁሉ መፍጠር አለባችሁ። ስለዚህ በዚህ ክፍል ውስጥ የምትማሩትን ትምህርት በግል ኑሮአችሁ ከህይወታቸሁ ጋር ለማዘመድ የሚትችሉበትን አገናኝ መንገዶችን ሁሉ ፈልጉ። ማረጋገጫ ይሄ እጥር ምጥን ያለ ክፍል ከትምህርቱ ውስጥ የተውጣጡና በሳምንቱ ውስጥ ልናደረጋቸውና ልንመሰክራቸው ወይም ልናውጃቸው የሚገቡ ትምህረቶችን መርሆችንና እውነቶች የያዘ ክፍል ነው። ጸሎትበዚህ ክፍል ውስጥ በቤተክርስቲያን ታሪክ ውስጥ ከያንዳንዱ ትምህርት ጭብጥ ጋር የተያያዙትን ልመናዎች እና የጸሎቶች ዓይነቶች ምን እንደሚመስሉ ለማየት እንዲረዳችሁ በቤተክርስቲያን ታሪክ ውስጥ ትልቅ ስፍራ ካላቸው እና ከሚታወቁ ቁልፍ ሰውዎች ጸሎታቸው እንዲካተት ተደርጓል። የልብ ጩኸት ለጌታ ይህ በትምህርቱ መጨረሻ ላይ መጸለይ ያለብህ ጸሎት ነው። ጸሎቶች በተለያዩ መልክ ሊቀርቡ ይችላሉ። ለምሳሌ ልክ በመፅሐፍ ቅዱስ ውስጥ እንደሚገኙት መዝሙርዎች በጽሁፍ የተነደፉና በፅሁፍ መልክ ሊደረጉ ይችላሉ አልያም ደግሞ በፈቃደኝነት ወዲያው ሊደረግ ይችላል። እነዚህ ጸሎቶች ጌታ በዚህ ትምህርት ለሚያስተምረን እውነት ፀጋን ለመቀበል እና በህይውታችን እንድናዛምድ የሚያስፈልገንን የተለየ አቅም እንድንጠይቅ ይረዱናል። እነዚህ የትህትና የአቅርቦትና የመተማመን ፀሎቶች ናቸው። በመሆኑም መንፈስ ቅዱስ እንደሚመራህ በጸጥታ ይሁን በጩኸት ጸልይ፡፡
ተጨማሪ ጥናት ይህ ክፍል በእያንዳንዱ ክፍለ ጊዜ ውስጥ በተማርካቸው ርዕሶች ላይ የበለጠ ለማወቅና ለማዳበር የምትፈልጉ ከሆነ ተጨማሪ ጥቆማዎችን የምንሰጥብት ክፍል ነው፡፡
ለሚቀጥለው ክፍለ ጊዜ ይህ ክፍል በቀጣዮቹ ምዕራፎች ወይም ክፍሎች ውስጥ የሚዳሰሱትን የትምህርት ይዘቶች እና ገጽታዎችን አጭር እና ግልጽ በሆነ ሁኔታ ቅድመ ዕይታን ይሰጣል።
የመጽሐፍ ቅዱስ የቃል ጥናት ቃሉን በልባችን ውስጥ ብንሸሽገው (ብናሰላስልውና/ ብናጠናው) በጌታ ላይ ኃጢአት አንሰራም የሚል ፅኑ እምነት አለን (መዝ. 119፡11)። ቃሉን ከልብ ማወቅ ማለት የልብ ማበረታቻ እና የጠላት ውሸቶችን ለመከላከል ዝግጁ የሚደርገን አቅም ነው፡፡ ስለዚህ እያንዳንዱ ክፍለ ጊዜ አንድ የማስታወሻ ጥቅስ ይዟል። ስለዚህም የተማራችኋቸውን እውነቶች ሊያስታውሳቸሁ የሚችል እና ቢያንስ በሳምንቱ እና በሚቀጥሉት ሳምንቶች ውስጥ አካሄዳችሁን ለማቅናት እንዲረዳችሁ የሚስችል ቢያንስ አንድ መጽሐፍ ቅዱስ ክፍል ወይም ጥቅስን አካትቷል። የቤት ሥራዎች ይህ የመጨረሻ ክፍል ትምህርቱን በሚያጠናቅቁበት ወቅት እንዲሰሯቸው የተወሰኑ “የቤት ስራዎችን” ያካትታል፡፡ እነዚህ ጠቃሚ እና ተግባራዊ ስራዎች ናቸው፡፡ እነዚህን ሃላፊነቶች በተግባር ላይ የምታውሉ ከሆነ በቁም ነገር የምትይዙዋቸው እንዲሁም በጥልቀት እና በጥሩ ሁኔታ ለማከናወን ከፍተኛ ጥረት ካደረጋችሁ ትምህርቱን መማራችሁ በጣም ፍሬያማና ውጤታማ ያደርጋችኋል። የቤት ስራዎቹ የተዋቀሩትም ያጠኑትን ትምህረት መሰረት በማድረግ በክርስቶስ ለማደግ እንዲረዳዎት ነው፡፡ ሥለዚህ እባክዎ የቤት ስራዎትን ያጠናቁ በአፋጣኝ/ በአፅንዎት/
Made with FlippingBook - Online magazine maker