Fight the Good Fight of Faith, Amharic Edition
12 • መልካሙን የእምነት ገድል ተጋደሉ
ይከታተሉ፡፡ ይህም ከማሰብ በዘለለ ትምህረቱንና ስራዎቹን ተግባራዊ ባደረጉ ቁጥር የመማር ሂደትዎን በላቀ ሁኔታ ያሻሽለዋል፡፡
መልካሙን የእምነት ገድል መጋደል፦ ይፋ በሆነው የእግዚአብሔር ትዕይንት ውስጥ የግል ድርሻን መወጣት (የተቀደሰው መሰረት የክትትል ስርዓተ- ትምህርት) ክርስቲያን መሆን ማለት የእግዚአብሔርን ታሪክ መቀላቀል ነው፡፡ ይህም እግዚአብሔር ሁል ጊዜ የሚናገረውና የሚያሳካው ታሪክ ማለት ነው! የእግዚአብሄር የመቤዠት እና የፍቅር፤ የደህንነት እና ተስፋ፤ የውጊያ እና የድል ታሪክ አሁን የእናንተ ታሪክ ሆኗል፡፡ የዚህ የተቀደሰው መሰረት የክትትል ስርዓተ- ትምህርት ታሪክ ወደ ዘመናት ጅማሬ ይመልሰንና ከዚያም በክርስቶስ የንግሥና ግዛት ወደተነገረው የከበረ መንግስት ተስፋን ይውስደናል። በጌታ በኢየሱስ በማመናችሁ ከኃጢአት ከቅጣት እና ከባርነት ነፃ ወጥታችኋል እንዲሁም በጦርነቱ ተሳታፊ እንድትሆኑ ተመርጣችኋል፡፡ በዚህ የመማሪያ መጽሐፍ ውስጥ የእግዚአብሔርን ዕቃ ጦር ሁሉ እንዴት እንደምትታጠቁ፣ የጠላት ሽንገላዎችን እንዴት እንደምትለዩ እና ከአማኞች ጋር እንዴት ማደግ እንደምትችሉ ትማራላችሁ፡፡ በዚህ ውጊያ ውስጥ ተሳታፊ እንዲሆኑ ተመዝግበዋል ስለዚህ መንፈሳዊ ተጋድሎን እንዴት መጋደል እንዳለቦት ማወቅና የተጋድሎውም ድል ሁሉን ድል ለነሳው ጌታ መሆኑን ማወቅ ይኖረቦታል፡፡ መንፈሳዊ ውጊያን በተመለከተ ብዙ የፃፈ ፓስተር ጆን ኤልድሬጅ እንዲህ ብሏላ “”የህይወትዎ ታሪክ እርስዎ ምን ሊሆኑ እንደሚችሉ በሚያውቅና- በሚፈራ አካል እና በልበዎ ውስጥ የረጅምና በጭካኔ የተሞላ የጥቃት ታሪክ ነው።’’ ይላል። እግዚአብሔር በቤተሰቦቻችሁ በጓደኞቻችሁ በዙሪያችሁ ባሉትና በጎረቤታችሁ ፊት ክርስቶስን ለመወከል ስትማሩ አምላክ ለእናንተ ያደረገውን ለእናንተ የሰውርውን ርስት ምን እንደሆን ማን ያውቃል፡፡ ስልዚህ ውጊያ ማድረግን መማር አለብዎት፡፡ ይህ የክርስትና ሕይወትን እንዴት በትክክለኛው ዕይታ ማየትና መልካመን የእምነት ገድል መጋደል የሚያስችሎትን መሳሪያዎች ለመርዳት የተነደፈ “የክትትል” ስርዓተ-ትምህርት ነው፡፡ ይህ የመመሪያ መጽሐፍ “እንዴት” የሚለውን ሃሳብ ያሳይዎታል፡፡ ስቱ ዌብበር የተባለ ጡረተኛ የጦር መኮንን እና አሁን ፓስተር የሆነ አገልጋይ በክርስትና ገና አዲስ ለሆኑትም ሆን በመንፈሳዊ ውጊያ ልምድ ላላቸው ለእያንዳንዱ ክርስቲያን በየእለቱ ስልሚጋፈጠው የምንፈሳዊ ውጊያ ባህሪ እንዲህ በማለት ፅፏል እያንዳንዱ ክርስቲያን የሚንቀሳቀስ የጦር ሜዳ ነው፡፡ እያንዳንዱ አማኝ በውስጡ አስፈሪ ግጭትን በጥልቅ ተሸክሞአል። እናም አብዛኞቻችን ውጊያውን እንድናሸንፍ የሚረዳን ነገር ለማግኘት ማንኛውንም ነገር እንሞክራለን። ይህንን በፈለጋችሁት ስያሜ ልትሰይሙት ትችላላችሁ፤ በስጋ እና በመንፈስ መካከል የሚደረግ ጦርንት ብለው ይጥሩት ወይም ለክርስቲአናዊ ህይወት ድል የሚደረግ ፍለጋ አልያም ያሻችሁን ስያሜ መሰየም ትችላላችሁ። ነገር ግን ይህ ቤት-አልባ- ወደታች- ጎትቶ- የሚጠል- ውጊያ ነው። እናም ሲጠናቀቅ አሁንም በጽናት ከቆሙት መካከል መሆንን ያስመኛል ወይም ትፈልጋላችሁ። የጦርነት መርሆዎች በመላው ዓለም በሚገኙ ወታደራዊ ማሰልጠኛ ተቋሞች ውስጥ ይሰጣሉ። በአብዛኛዎቹ መንገዶች መንፈሳዊ ውጊያ ከወታደራዊ ጦርነቶች ፈጽሞ የተለየ አይደለም፡፡ እያንዳንዱን ወታደር በህይወት የሚያቆየውን መርሆችን መረዳት ብቻ ሳይሆን አሸናፊ ለመሆን የሚጠበቅበትን መርሆዎች መማርና በየዕለቱ ተጋድሎ ውስጥ መተግበር ይጠበቅበታል። ምክንያቱም “መጋደላችን ከደምና ከሥጋ ጋር አይደለምና፥ ከአለቆችና ከሥልጣናት ጋር ከዚህም ከጨለማ ዓለም ገዦች ጋር በሰማያዊም ስፍራ ካለ ከክፋት መንፈሳውያን ሠራዊት ጋር ነው እንጂ” (ኤፌሶን 6, 12ለ)
~ Stu Webber. Spirit Warriors. Sisters, OR: Multnomah Publishers, 2001, p. 16.
Made with FlippingBook - Online magazine maker