Fight the Good Fight of Faith, Amharic Edition
ተጨማሪ መግላጫ • 133
ተጨማሪ ማብራሪያ 9 ጥገኛ የመሆናችን መግለጫ፡ ነጻነት በክርስቶስ ሬቨ. ዶ/ር ዶን ኤል. ዳቪስ
ለክርስቲያኖች ክርስቶስ በመስቀል ላይ በሞቱበት ነጻነት ውስጥ እንዲሁም ወደ ቤተክርስቲያን ሕይወት እና ተልዕኮ ውስጥ የመንፈስ ቅዱስ መምጣት ክልል ውስጥ ክርስቲያናዊ ሥነ-ምግባርን ማስተማር አስፈላጊ ነው (ማለትም ገላትያ 5፡1 “በነጻነት ልንኖር ክርስቶስ ነጻነት አወጣን”) እናም ሁልጊዜም ነፃነታችሁን እግዚአብሔርን ለማክበር እና የክርስቶስን መንግሥት ለማስፋፋት በመጠቀም አውድ ውስጥ መሆን ነው። በመልዕክቱ ውስጥ ካሉ አንዳንድ ወሳኝ የነጻነት ጽሑፎች መሰረት በ1ኛ ቆሮንቶስ የተሰጡትን “6-8-10” መርሆዎችን በማጎልበት ለክርስቶስና ለመንግሥቱ ለመኖር እና ለሁሉም የሞራል ጉዳዮችን ለመተግበር ማስተማር እንደምንችል አምናለሁ።
1. 1 ቆሮ. 6፡9-11 - ክርስትና ክርስቶስን ወደ መምሰል ስለመለወጥ ነው። ምንም ዓይነት ሰበብ ሊሆን የሚችል ሰው ወደ መንግሥቱ አይገባም
2. 1 ቆሮ. 6.12 ሀ - በክርስቶስ ነፃ ነን; ነገር ግን ሁሉም ነገር የሚያንጽ ወይም የሚጠቅም አይደለም።
3. 1 ቆሮ. 6፡12ለ - እኛ በክርስቶስ ነፃ ነን ነገር ግን ሱስ የሚያስይዝ እና እናንተን የሚቆጣጠር ማንኛውም ነገር ሁሉ ክርስቶስንና መንግሥቱን ይቃወማል።
4. 1 ቆሮ. 8:7-13 - እኛ በክርስቶስ ነፃ ነን ነገር ግን ይህ ነፃነታችን በክርስቲያኖች ዘንድ በተለይም ህሊናቸውን ደካማ እና በቀላሉ ሊሰናከል የሚችሉትን ለደካሞች ዕንቅፋት እንዳይሆንባቸው ልንጠነቀቅ ይገባል።
5. 1 ቆሮ. 10:23 በክርስቶስ ነፃ ነን; ሁሉ ተፈቅዶልኛል፥ ሁሉ ግን የሚጠቅም አይደለም፤ ሁሉ ተፈቅዶልኛል፥ ነገር ግን ሁሉ የሚያንጽ አይደለም።
6. 1 ቆሮ 10፡24 - እኛ በክርስቶስ ነጻ ነን እናም ነፃነታችንን በክርስቶስ ወንድሞቻችንንና እህቶቻችንን እንድንወድ እና ሌሎችን ለመንከባከብ ልንጠቀምበት ይገባል (ገላ 5.13) ።
7. 1 ቆሮ. 10፡31 እኛ በክርስቶስ ነጻ ነን እናም ይህ ነጻነታችን በምንበላው ወይም በምንጠጣው ወይም ማናቸውንም ነገሮች ስንሠራ ሁሉን ለእግዚአብሔር ክብር እንድናደርግ ተሰጥቶናል።
8. 1 ቆሮ. 10፡32-33 - እኛ በክርስቶስ ነፃ ነን እናም ይህንን ነጻነታችንን በዓለም ውስጥ ወይም በቤተክርስቲያን ውስጥ ለሚገኙ ሰዎች እንዳንሆንና ይልቁንም አዎንታዊ ተጽዕኖ በመፍጠር ሰዎች ሁሉ ክርስቶስን እንዲያውቁ እና እንዲወዱ ማድረግ የምንችለውን ሁሉ እናደርጋለን ይህም ማለት እነርሱ ወደ ድነት እንዲመጡ ማድረግ ነው።
ከእነዚህ መርሆዎች በተጨማሪ, እኛ ደግሞ የሚከተሉትን መርሆዎች አፅንዖት መስጠት እንዳለብን አምናለሁ
• 1 ጴጥ. 2፡16 አርነት ወጥተን እንደ እግዚአብሔር አገልጋዮች ልንኖር እንጂ ያ አርነት ለክፋት መሸፈኛ እንዲሆን አታድርጉ።
Made with FlippingBook - Online magazine maker