Fight the Good Fight of Faith, Amharic Edition

ትምህርት 1 ራሳችንን የምናገኝበት የህይወት መድብል ታሪካችን በእግዚአብሔር ታሪክ ውስጥ

በእግዚአብሄር አጠቃላይ ጥበብና ማስተዋል ለምናምን የእግዚአብሔር የተትረፈረፈ ጸጋ በእኛ ላይ ታይቷል፡፡ የፈቃዱን ምሥጢር አስታውቆናልና፤ ይህም በራሱ ዓላማ የተያዘ በክርስቶስ የነበረ ነው፣ በዘመን ፍፃሜ የተገለጠ ክቡር ዕቅዱም ማለትም እግዚአብሔር በሰማይ እና በምድር ያሉትን ነገሮች ሁሉ ጨምሮ ሁሉንም ነገሮች በክርስቶስ አንድ ለማድረግ ነው፡፡

~ ጳውሎስ ለኤፌሶን (ኤፌ 1.8-10

በዚህ ክፍለ ጊዜ መጨረሻ ላይ የሚከተሉትን ዋና ዋና ሃሳቦች በማመን ራሳችንን የምናገኝበት የህይወት መድብል ምን እንደሆነ እንረዳለን • የዓጽናፈ ዓለሙ አምላክ ፣ ሁሉን ቻይ ጌታ፣ እውነተኛና ዘላለማዊ አንድ አምላክ በሦስት አካላት ማለትም አብ፣ ወልድና፣ መንፈስ ቅዱስ አንድ አምላክ እንድሆነ በማወቅ • እግዚአብሔር የሁሉ ነገሮች ፈጣሪ፣ የሚታዩትን እና የማይታዩትን እንዲሁም ሰውንም በመልኩና በአምሳሉ የፈጠረ እንደሆነ በማወቅ • በሰይጣን ዓመፅ* እና በመጀመሪያዎቹን ሰብዓዊ ጥንዶች * ምክንያት ፍጥረቱ ሁሉ እንደተረገመ ነገር ግን እግዚአብሔር ክፋትን ለማሸነፍ እና ሁሉንም ነገር በአዳኙ በጌታ በኢየሱስ ክርስቶስ በኩል ለማዳን ዕቅድ እና የተስፋ ቃል እንደሰጠ በማወቅ ዘለአለማዊው አምላክ አባቴ ሆይ በቃልህ እንደተናገርክ አንተ የእውቀት እና የጥበብ ሁሉ ምንጭ ነህ፡፡ ይህም እውነት መሆኑን አምናለሁ፣ ውድ አባቴ ሆይ የእውነትን ቃል በትክክለኛ መንገድ ማከፈል እንድችል መለኮታዊ ጥበብ እንድትሞላብኝ እጠይቅሃለሁ (2ኛ ጢሞቴዎስ 2፡ 15)። እባክህ የምሄድበትን መንገድ ምራኝና አስተምርኝ (መዝሙር 32፡8) እርምጃዬንም አቅና። ድምፅህን ለመስማት ጆሮዬን አዘንብል አስተሳሰቤን እና ንግግሬን አቅና እንዲሁም ከስህተት በመመለስ በትክክለኛው መንገድ ምራኝ። አባት ሆይ የማስተዋል እና የመለየትን ስጦታን እንድትሰጠኝ እና ቃልህንም በምማርበት ጊዜ በእውነተኛውና በሃሰተኛው ትምህርት መናፍስትና ጸጋዎች መካከል ያለውን ልዩነት እንድረዳ እርዳኝ። በመንፈስ ቅዱስህ ፈቃድህን አሳየኝ ፈቃድህንም በሙሉ ልቤ መቀበልና መያዝ እንድችል ማስተዋል ስጠኝ። ጌታ ሆይ እባክህን ለመስማት እና ለማዳመጥ የፈጠንሁ፤ ለመናገርና ለቁጣ የዘገየሁ እንድሆን እርዳኝ (ያዕቆብ 1፡19)። የአፌም ቃልና የልቤ አሳብ በአንተ ዘንድ ተቀባይነት ይኑራቸው። ሰው ሁሉ እውነትህ ሊረዳና ሊያተርፍበት እንዲችል እውነትህን የምናገርበትን ጥበብን ሥጠኝ።

ዓላማዎች

የመክፈቻ ጸሎት-ለጥበብ

* ሰይጣን - ሰይጣን የዲያቢሎስ የግል መጠሪያ ስሙ ነው፣ የእግዚአብሔር እና የሰው ልጅ ባላጋራም ነው። *ሰብዓዊ ጥንዶች - አዳምና ሔዋን በእግዚአብሔር መልክና አምሳል ከእግዚአብሄር ጋር በህብረት እንዲኖሩ፣ ትርጉም ያለው ስራን ለመስራት እና በእግዚአብሔር ፍጹም ዓለም ያለውን ሃብት እየተደሰቱ እንዲኖሩ የመጀመሪያዎቹ ወንድ እና ሴት ሆነው የተፈጠሩ ናቸው፡፡

15

Made with FlippingBook - Online magazine maker