Fight the Good Fight of Faith, Amharic Edition

22 • መልካሙን የእምነት ገድል ተጋደሉ

የኒቂያው የሃይማኖት መግለጫ (ተጨማሪ አባሪ 24 እና 25) የሐዋርያት የሃይማኖት መግለጫ (ተጨማሪ አባሪ 26)

ይህ ዓለም የትዕይንት መድረክ ነው ይባላል። “ከዘመናት ግጭት” ከሚባሉት ትላልቅና አስደናቂ ታሪኮችና ክስተቶች የተሻለ ይህንን እውነትነት በግልጽ ሊያሳይ የሚችል የለም። ቅዱስ ቃሉ እና ታሪክ በግልጽ እንደሚያሳዩን በሁለት መንግሥታት መካከል የተጀመረ ጦርነት እንዳለ እና እኛም በእግዚአብሔር ዕቅድ አማካኘንተ የራሳችንን ሚና እንደምንጫውትና ተሳታፊ እንደምንሆን ያሳየናል። በመሆኑም በዚህ የእግዚአብሄርን መንግስት ዓላማ በሚቃውም ታሪካዊ ግጭት ዳራ ውስጥ ሆነው ነው የመጽሐፍ ቅዱሳዊ ጸሐፊዎች ቅዱሳት መጻሕፍትን ለመጻፍና ለመተርጎም ጥረት ያደረጉት።

~ ጄምስ ደ ዩንግ እና ሣራ ሀሪ ከታዋቂው ባሻገር. ጌርስሃም ኦቲ: ቪዥን ሃውስ ማተሚያ 1995 ገጽ 83-84.

10ሀ ሁሉን ቻይ የሆነው እግዚአብሄር አምላክ በናዝሬቱ ጌታ በኢየሱስ ክርስቶስ አማካኝነት ወደ ምድር መጣ በመስቀል ሞቱም የሰውን ልጆች በሙሉ ከራሱ ጋር አስታረቀ (2 ኛ ቆሮንቶስ 5፡19)።

ቁልፍ መርህ

ከዚህ በታች በተመለከቱት ክርክሮች እና ጽንሰ ሐሳቦችን ያንብቡ እና ያብራሩ፤ እንዲሁም ከላይ በተማራችሁት የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል በመመርኮዝ ተገቢውን ምላሽና ይስጡ የእርሶንም መረዳት ያጋሩ። 1. “አምላክ አለ ብዬ አላስብም” በምሳ ሰዓት ላይ ነበር ጃኒስ ከሥራ ባልደረባዋ ሊያ ጋር ዓለም እንዴት እንደተፈጠረች የሚለውን ሃሳብ ሲወያዩ ከሊያ የሰማቸው። ሊያ እግዚአብሄርም ሆነ ሌሎች አማልክት በዓለም ላይ መኖሩን የሚያረጋግጥ ምንም ማስረጃ የለም የሚል ፅኑ እምነት አላት። ሁሉም ሃይማኖቶች እግዚአብሔር ማን እንደሆነ ምን ያህል አማልክት እንዳሉ እና እንደ ቅዱስ መጽሃፍት የሚቆጠሩትን በተመለከተ የተለያየ ሃሳብ አላቸው ትላለች። ጃኒስ በክርስቶስ የምታምን አማኝ ናት፤ ሁሉን ቻይ የሆነ እግዚአብሄር አብም ዓለምን እንደፈጠረ እና ያም ፍጥረት ያለ ምንም ዓላማ ወይም ትርጉም እንኳን እጅግ በጣም ቆንጆ እና ድንቅ ነው ትላለች። እናንተ ጃኒስን ብትሆኑ ከሊያ ጋር መጽሐፍ ቅዱስ ስለ እግዚአብሔር እና ስለ ዓለም አፈጣጠር ምን እንደሚል አሁን ያነበቡትን የቅዱስ መጻሕፍትን መሰረት በማደረግ ትገልጹታላችሁ፡፡ ፈጣሪ ከሆነ እና ሁሉንም ነገሮች በአንድነት የሰራና የሚቆጣተር ከሆነ ለምንድን ነው ታዲያ በዓለም ላይ አሰቃቂ ነገሮች የሚከሰቱት?” አንዳንዶች እግዚአብሔር በዓለም ውስጥ ስለሚከናወኑት ነገሮች ምንም እንደማያውቅ ይከራከራሉ ሌሎች ግን እግዚአብሔር እንደሚያውቅ ቢናገሩም በሚሆኑት ነገሮች ላይ ግን ጣልቃ ላለመግባት ወስኗል ይላሉ። እስካሁን በተማራችሁትና በምታውቁት ላይ በመመርኮዝ አሁን አሁን በዓለም ላይ ስለሚሆኑት ነገሮች ለምን እንደዚህ ሆኑ ለሚለው ጥያቄ ምን ምላሽ መስጠት ትችላላችሁ? በዚህ ትምህርት ውስጥ የተማርነው ቢያንስ ለአጭር ጊዜ በችግሮች ውስጥ እንድናለፍ የምንደረገው ለምን እንደሆነ ለመረዳት ምን ያህል ይረዳናል? 2. “ እግዚአብሄር አምላክ ታዲያ ነገሮችን ለምን አሁን አይለውጣቸውም?” ከአንዳንድ አዳዲስ ክርስቲያኖች ጋር በአንድ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት ውስጥ የመጣ ጥያቄ ነበር። “እግዚአብሔር

የናሙና ጥናቶች

Made with FlippingBook - Online magazine maker