Fight the Good Fight of Faith, Amharic Edition
ትምህርት 1 ራሳችንን የምናገኝበት የህይወት መድብል • 23
3. ወደ እግዚአብሔር የሚወስዱ ብዙ መንገዶች አልነበሩምን? በዚህ ዘመን ያሉ ብዙ ሰዎች ሁሉም ሃይማኖቶች እኩል እንደሆኑና ወደ እግዚአብሄር አምላክ የሚያደርሱ ብዙ የተለያዩ መንገዶች እንዳሉ ያምናሉ። ልክ ከተራራ ግርጌ ዙሪያ ከተለያየ ቦታ በመነሳት ወደ ተራራው ጫፍ ለመሄድ የተሰባሰቡ ብዙ የተለያዩ ቡድኖች ያመለክታሉ ይላሉ። ሁሉም ወደ ተራራው ጫፍ (መለኮታዊ” ህይወት) ለመድረስ ግን በመንገዱ ላይ ባሉት የተለያዩ አቅጣጫዎች ማለተም በተለያዩ አመለካከቶች የሚመጡ ናቸው ይላሉ። በቅርብ ወይም ዘግይቶ (ክርክሩ ይቀጥላል) ሁሉም ወደ ተራራው የሚወጡ ሰዎች (የዓለም ሃይማኖቶች) ከተራራው ጫፍ ላይ መንገዳቸውን (መንፈሳዊነትና መለኮትን) ያገኙታል። በዚህ አመለካከት ሁሉም ሃይማኖቶች እኩል ናቸው ሁሉም መለኮታዊውን ቃል ይናገራሉ እና ሁሉም እግዚአብሔርን ለማግኘትና ለመከተል ይችላሉ። የእኛ ጥናት ለእንደዚህ ዓይነቱ አመለካከት/ በርካታ መንገዶች አሉ ለሚለው አመለካከት/ እንዴት ሊናገርና ሊረዳ ይችላል? አሁን ግን ንስሃ በመግባት(ከኃጢአት ጎዳና በመፀፀትና በመመለስ) የናዝሬቱ ኢየሱስን የህይውታችሁ ጌታ አድርጋችኋል፤ በወንጌለም እምነት አማካኝነት ከላይ ተወልዳችኋል የእግዚአብሔርም ልጆች ሆናችኋል። ይህም ማለት ለእግዚአብሔር ክብር የሰውን ዘር ለማዳን ባለው ታላቅ ዕቅዱ ውስጥ እንድተሳተፉ ተመርጣችኋል ማለት ነው፡፡ አሁን የእግዚአብሔርን ዕቅድና ታሪክ በማንበብ ላይ ብቻ አይደለም ያላችሁት ይልቁንም አሁን ዕቅዱን ተቀላቅላችኋል! አሁን በእምነት ከክርሰቶስ ጋር ተቀላቅላችኋል እናም ኃጢያታችሁ ሁሉ ይቅር ተብሏል፤ የእግዚአብሄርም ቤተሰብ ሆነዋል ወደ እርሱ ሠራዊትም ተቀላቅለዋል። በጌታ ኢየሱስ ባመናችሁ ጊዜ የእግዚአብሄርን ታላቅ ታሪክ ተቀላቅላችኋል! በመሆኑም አሁን ስለዚህ ታላቅ ታሪክ ማወቅ ያስፈልግዎታል፤ እግዚአብሔር ምን እንደሚያደርግ እንዴት እንድትኖሩ እንደሚፈልግ እና ሌሎችን ወደ እርሱ የፍቅር እና የመዳን ታሪክ እንዲቀላቀሉ እንዴት ሊጠቀምባችሁ እንደሚችል ማወቅ ያስፍልጋችኋል። አትፍሩ! እግዚአብሔር እናንተን ለማስተማር ቅዱስ መንፈሱንና የቤተክርስቲያን ወንድሞቻችሁን ወዳጆቻችሁ እንዲሆኑና ይህን ታላቅ ታሪክ ለመኖር የሚያስፈልጋችሁን መንፈሳዊ አቅርቦትን ሁሉ ለማሟላት እንዲረዳችሁ የጸሎት ኃይል ሰጥቷችኋል። አሁን አዳዲስ ወዳጆችና እና አዳዲስ ጠላቶች አሏችሁ! እግዚአብሄር ከጨለማ ኃይልና ጉልበት አድናችኋል በመሆኑም አሁን የሰይጣንን ውሸቶች፣ የዓለምን ፈተናዎች እና የድሮ የኃጢያት ባህሪያችሁን መከልከልን መማር አለባችሁ። መዳን ማለት በሁሉም ስፍራ ለሚገኙ የሰው ልጆች ልብንና አእምሮን ለማስታረቅ የእግዚአብሔርን ወገን መሆን ማለት ነው። ነገር ግን አትጨነቁ! እግዚአብሄር የክርስትናን ህይወት እርሱን ለማስደሰትና ለማክበር እንድንኖርና በዚህ ታላቅ ታሪክ ውስጥ ጠላትን ድል ለምነሳት የሚያስፈልገንን ሁሉ ሰጥቶናል። በመሆኑም እግዚአብሄር ወደ ራሱ ስላሰጠጋችሁ ልጆቹም ስላደረጋችሁና የዘላለም ህይወት ስለሰጣችሁ ጊዜ ውስዳችሁ አመስግኑት አክብሩትም። እንደ ጌታ ኢየሱስ ደቀመዝሙር (ተከታይ) ጥንካሬ እና እርዳታ እንዲለግሳችሁ መማር ማደግንና በሠራዊቱ ውስጥ እንደ ወታደር ሆኖ መቀጠል እንዲያስችላችሁ ጠይቁት። እርሱ ፈጽሞ አይተወንም አይጥለንም።
ግንኙነት
እንኳን ወደ ቤተሰቡና ወደ ውጊያው በደህና መጡ!
Made with FlippingBook - Online magazine maker