Fight the Good Fight of Faith, Amharic Edition
142 • መልካሙን የእምነት ገድል ተጋደሉ
19. አንድ አማኝ የተመረጠ ትውልድ፥ ቅዱስ ሕዝብ እና ለርስቱ የተለየ ወገን ነው - 1 ጴጥ. 2.9። ይህ በዚህ ዘመን የአማኞች ማህበር መሰረት ነው።
20. አማኝ ሰማያዊ ዜጋ ነው -ፊል. 3:20። ስለዚህ እርሱ/እርሷ ምድራቸውን በተመለከት እንግዶች ናቸው (1 ጴጥ 2,13)፤ እንዲሁም እርሱ/እርሷ በእውነተኛ ቤታቸው በሰማይ ለዘላለም በደስታ ይኖራሉ።
21. አማኝ በእግዚአብሔር ቤተሰብ ውስጥ የቤተሰቡ አባል ነው - ኤፌ. 2.1, 9 እሱ/እርሷ ከእውነተኛ አማኞች ብቻ የተዋቀረው የእግዚአብሔር “ቤተሰብ” አካል ናቸው።
22. አማኝ በቅዱሱ ኅብረት ውስጥ ነው (ዮሐንስ 17: 11, 21-23):: እሱ/እሷም አማኞች እርስ በእርሳቸው ኅብረት የሚያደርጉበት የቅዱሳን ህብረት አንዱ አካል ሊሆኑ ይችላሉ።
23. አማኝ በሰማያዊ ማህበር ውስጥ የተካተተ ነው - ቆላ. 3፡1; 2ቆሮ. 6.1; ቆላ. ዮሐንስ 14 12-14; ኤፌ. 5.25-27; ቲቶ 2 13. እርሱ/እርሷ ከክርስቶስ በተካፈሉት ህይወት ምክኒያት በመተባበር በአሁኑ ጊዜ በህይወት፣ በስልጣን፣ በአገልግሎት፣ በመከራ፣ በጸሎት የእክርስቶስን ዳግም ምጻት እንደምትጠብቅ እንደ ክርስቶስ ሙሽሪት ከእርሱ ጋር አብረው ሰራተኛ ናቸው። 24. አንድ አማኝ ወደ እግዚአብሔር አብ መግባት አግኝቷል - ኤፌ. 2.18. እርሱ/እርሷ በመንፈሳዊነት ማደግ እንዲቸል/ እንድትችል ወደሚያስችል ጸጋ መግባተን አግኝተዋል እንዲሁም ሁሉ ነገር በግልጽ በሚታይበት በጸጋው ዙፋን ፊት መግባት እንዲቸሉ መብትን አግኝተዋል(ዕብ 4፡16)። 25. አማኝ “እጅግ ብዙ” በሆነው የእግዚአብሔር እንክብካቤ ውስጥ ነው - ሮሜ. 5.8-10. እርሱ/ እርሷ የእግዚአብሔር ፍቅር (ኤፌ 2-9-9)፣ የእግዚአብሄር ጸጋ(ኤፌ. 2፡7-9)፣, የእግዚአብሔር ኃይል (ኤፌ 1፡ 19)፣ የእግዚአብሔር ታማኝነት (ፊል 1.6), የእግዚአብሔር ሰላም (ሮሜ 5፡ 1)፣ የእግዚአብሔር ማጽናናት (2ተሰ 2, 16-17) እና የእግዚአብሔር ምልጃ (ሮሜ 8.26) አካል ነው።
26. አማኝ የእግዚአብሔር ውርስ ነው - ኤፌ. 1.18. እርሱ/እርሷ ከእግዚአብሄር አብ ለክርስቶስ የተበረከቱ ስጦታ ናቸው።
27. አንድ አማኝ እግዚአብሔር የሰጠው ሁሉ እና እራሱ እግዚአብሄር ውርሱ ነው - 1 ጴጥ. 1፡4።
28. አንድ አማኝ በጌታ ብርሃን አለው (2 ቆሮ. 4፡6) እርሱ/እርሷ ይህን ብርሃን ብቻ ያላቸው ብቻ ሳይሆኑ ብቻ ሳይሆን በብርሃን እንዲጓዙ ታዘዋል።
29. አንድ አማኝ ከአብ፣ ከወልድና ከመንፈስ ቅዱስ ጋር በጥብቅ የተሳሰረ ነው - 1 ተሰ. 1፡1; ኤፌ. 4.6; ሮም. 8፡1; ዮሐንስ 14, 20; ሮም. 8.9; 1 ቆሮ. 2.12.
30. አንድ አማኝ በመንፈስ ቅዱስ ፍሬዎች ብርቱ ወይም በፍሬአማነት ተባርኳል - ኤፌ. 1.14; 8.23። እርሱ/እርሷ ከመንፈስ የተወለዱ(ዮሐንስ 3.6) እናም በመንፈስ ቅዱስ የተጠመቁ(1 ቆሮ 12.13) ይህም አማኙ ከክርስቶስ አካል ጋር ተጣምሮ ሁሉም ነገር “በክርስቶስ” እንዲካፈልና ክርስቶስ ያለውን ሁሉ እንዲካፈል መንፈስ ቅዱስ በህይወታቸው የሰራው ሥራ ነው። እንዲሁም ደቀ መዝሙርቱ በመንፈስ ቅዱስ የሚኖርባቸው(ሮሜ 8፡ 9)፣ በመንፈስ ቅዱስ የታተሙ (2 ቆሮ 1፡22)፣ እሱም/እሷ ለዘላለም በዋስትና እንዲኖሩ እና የእርሱ ኃይል እና ውጤታማነት በእነርሱ እንዲገላጥ በመንፈስ ቅዱስ ተሞልተዋል (ኤፌ 5.18)።
Made with FlippingBook - Online magazine maker