Fight the Good Fight of Faith, Amharic Edition
ትምህርት 1 ራሳችንን የምናገኝበት የህይወት መድብል • 17
(እግዚአብሄር አምላክ መኖሩን የሚክዱ) አምላክ እንዳለ ማመን ወይም ለሕይወት የሚሆን ትልቅ ዕቅድ አለ በሎ ማሰብና ማመን ሞኝነት ነው ይላሉ። እንዲሁም እግዚአብሔር ስለሌለ ዓጽናፈ ዓለሙ የራሱ የሆነ አሠራር ብቻ ነው ያለው፤ ለሕይወት እና ለዓለም ምንም ዕጣ ፈንታ ወይም ዓላማ የለም ብለው መከራከያ ሃሳብ ያቀርባሉ። አግኖስቲክስ (እግዚኣብሄር እንዳለ ማወቅ አንችልም ብለው የሚያምኑ) እግዚአብሔር ቢኖረም እንኳን እሱ/ እርሷ/ ነገር ይሁን አይሁን ልናውቅ አንቸልም፤ እኛ ልናደርግ የምንችለው የመጨረሻ ጥሩ ነገር - ምናልባት ነገሮች ወደ ጥሩ ይለወጣሉ ብሎ ተስፋ ማድረግ ነው! ብለው ያምናሉ። ታዲያ የሐዋርያትና የኒቂያ የሃይማኖት መግለጫዎች እግዚአብሄር እንደሌለ እና በዓጽናፈ ዓለም ውስጥ ምንም ዕቅድ እንደሌለው ለሚከራከሩ ሰዎችና ለሚሰነዝሩት ተቃውሞ ምላሽ ለመስጠት እንዴት ሊረዱን ይችላሉ? በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ላይ ያተኮረውን የእግዚአብሔርን እና የሰውን ዘር ታሪክ እናገኛለን። ነገር ግን ይህ ወሳኝ ታሪክ እኛ እንድናነበው የተቀመጠ ታሪክ ብቻ ሳይሆን ይልቁንም እኛ የምንሳተፍበት ክፍል ነው። የጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ተከታይ እንደመሆናችን መጠን አሁን አዲስ ማንነት አለን እናም እርስዎም ራስዎን በሚያገኙበት በዚህ ወሳኝ ታሪክ ውስጥ የራሶን ድርሻ ይወጣሉ። ዓጽናፈ ዓለሙ የተፈጠረው በሉዓላዊና* በሥሉስ* አምላክ ነው ማለትም በአብ በወልድና በመንፈስ ቅዱስ ነው። ከዘመናት በፊት በዘላለም ክብር ውስጥ የሚኖር እና ምንም የማይጎድለው እግዚአብሔር አምላክ በራሱ መልክና አምሳል የተፈጠረውን የሰውን ልጅ የፍጥረቱን ሙሉነት ሊለማመድ /ሙሉ በሙሉ ሊያገኝበት/ የሚችልበትን ዓለም ለመፍጠር መረጠ። ነገር ግን ይህ ዓጽናፈ ዓለም በዓመፀኛው መልዓክ* በሰይጣን መጣል ምክኒያት በጥፋት ተውጦ ነበር። ሰይጣን የእግዚአብሔርን መንግሥት ለመገልበጥ በማቀድ የመጀመሪያዎቹን ሰብዓዊ ጥንዶች (አዳምና ሔዋን) በእግዚአብሔር ላይ በማሳመፅ የሰውን ዘር በመርገም ስርና እንዲውድቁ እና የመዳንን ተስፋ አሳጥቶ እነዲኖሩ አደረጋቸው። በዚህ ዓመፅ ፊትለፊት እግዚአብሔር ይህንን ውድቀት የሚያስተካክል እና እርግማን ያስከተለውን ውጤት ለዘላለም የሚያስወግድና የሚቤዥ አንድ ድል አድራጊና አዳኝ ለማስነሳት ቆርጦ ነበር። በአብርሃም በኩል እግዚአብሔር ይህንን መሲህ (የተቀባ) ለማምጣት እና መሲሁ የሚመጣበትን ሕዝብ (እስራኤልን) ለማስነሳት ቃል ኪዳን ገባ። እናም የዘመኑ ፍፃሜ በደረስ ጊዜ እግዚአበሄር አብ ክብሩን ለመግለጥ ሕዝቡን ለማዳን እና ፍጥረቱን ለመዋጀት አንድያ ልጁን ኢየሱስ ክርስቶስን ላከው። ጌታ ኢየሱስም በትምህርቱና በተዓምራቶቹ አማካኝነት የእግዚአብሄርን መንግሥት ጥበብና በኃይል በሙላት ገልጧል። በመስቀል ላይ ውድ ሕይወቱን በፈቃደኝነት በመስጠቱ የኃጢአታችን* ቅጣት ከፈለ፤ የዲያቢሎስንም ስራዎች ሁሉ አጥፋ። እግዚአብሔርም ኢየሱስ ክርስቶስን ከሙታን አስነሳው፤ ከአርባ ቀንም በኋላ ጌታም በድል አድራጊነት ወደ ሰማይ ዓረገ። ከትንሣኤው በኋላ
ይዘት
*ሉዓላዊው - በተፈጥሮና በታሪክ ጉዳዮች ላይ ቁጥጥር ማድረግ የሚችል ገደብየለሽ ወይም ልዑል ኃይልን ያመለክታል *ሥላሴ - ሦስትዮሽ - “በሶስት አካላት የተገለጠን አንድ አምላክ” የሚለውን ሃሳብ በሌላ መንገድ የመግለጫ መንገድ ነው። አንዳንድ ጊዜ “ሥላሴ” የሚለው ቃል አንድ አምላክ ነገርግን ሦስትን ብቻ ስለሚያመለክት ነው፡፡ *መላዕክት - መላዕክት ከሰው ልጆች በላይ ታላቅ ኃይል እና የማሰብ ችሎታ ያላቸው በእግዚአብሔር የተፈጠሩ ፍጡራን ናቸው። *ኃጢያት - ኃጢያት ማለት እግዚአብሔር የሚፈልገውን ነገር በምንናገረው አልያም በምንሰራው ወይም በምናስብበት ነገር ከማድረግ መጉደል ማለት ነው። *ወደ ሰማይ መውጣት - ኢየሱስ ምድሪቱን ትቶ በአካል ተከታዮቹም እያዩ ወደ ሰማይ ሄደ። ከሞቱና ከትንሳኤው በኋላ ዕርገቱ በዚህች ምድር ድል መንሳቱንና በሰማይም እንደ ድል አድራጊ ንጉሥ በመሆን በዙፋኑ ላይ መቀመጡን ያሳያል፡፡ በተጨማሪም በዓለም ዙሪያ ያሉትን ክርስቲያኖች ሁሉ ኃይልን ሊያቀዳጅ የሚችል የመንፈስ ቅዱስ መምጣትም አቀናጅቷል።
Made with FlippingBook - Online magazine maker