Fight the Good Fight of Faith, Amharic Edition
18 • መልካሙን የእምነት ገድል ተጋደሉ
በሃምሳኛው ቀን እያደግች የነበረችውን የኢየሱስን ክርስቶስን ካምፓኒ ማለትም ደቀ መዛሙርትን* ወይም ቤተክርስቲያን* በኃይል ለማስታጠቅ መንፈስ ቅዱስን ላከላቸው። እንደ እግዚአብሔር አብ ቤተሰብ የክርስቶስ አካል እና የመንፈስ ቅዱስ ቤተመቅደስ እንደመሆናችን መጠን ቤተክርስቲያን በሁሉም ስፍራ የሚገኙ ሰዎችን ሁሉ በዚህ ወሳኝ ታሪክ እንዲካፈሉ ለመጋበዝ ተወክላለች። በእምነት የምናደርገው መልካሙ ገድል ሲጠናቀቅ ጊታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሃዘንን በሽታን እና ሞትን የሚጠፋባትን የእግዚአብሔርን መንግሥት በመላው ጽንፈ ዓለም ውስጥ ለመመስረት ይመጣል ከሕዝቡም ጋር ለዘላለም ይነግሣል ለስሙ ክብር ይሁን! በተለይ ወደ መፅሐፍ ቅዱስ ታሪክ ስንሸጋገር እነዚህ ጥያቄዎች አንገብጋቢ ሊሆኑ ይገባል ምክኒያቱም ይህን የመቀልበስ ስራው በእጥፍ ወይም በሦስት እጥፍ ሊሆን ይችላል። በእነዚያ የታሪክ መጽሐፍት እና በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ያሉትን ታሪኮች አንድ ገፅ በገለጥን ቁጥረ ፈተናውን የመቀልበስ ስራ በተደጋጋሚ ይገጥመናል። ከመካከላችን አንዱ በሌላ ስፍራ እንደጻፋው ‘በታሪክ ወሳኝ ሁኔታዎች ውስጥ እግዚአብሔር ታላላቅ ተዓምራቶቹን በመግለጥ የራሱን ተፈጥሮ እና ፈቃዱን ሲገልጥ፤ እግዚአብሔር ድሆችን እና የተጨቆኑትን ለማዳንም ደግሞ ጣልቃ ገብቷል ማለት ነው::’ እግዚአብሄር ጣልቃ የገባባቸው ጊዜያቶችም እንዲሁ የመቀልበሻ ጊዜያቶች ናቸው፤ አንድ ሰው የሚጠብቀው ሳይሆን ያልጠበቀው ሲሆንለት በዓለም ያሉ ሰዎች እንደሚያስቡት እግዚአብሄር አላስፈላጊ መሆኑን ሳይሆን እርሱ ለዓለም በጣም አስፈላጊ እንደሆነ ያምናሉ።
~ ሮናልድ ሲርደር እና ማይክል ማኪ. አስጊ በሆነው ዓለም ውስጥ ሕይወትን መስበክ ፊላዴልፊያ-ዌስትሚንስተር ፕሬስ, 1987, ገጽ 56-57.
ከጌታ ኢየሱስ በስተቀር መጽሐፍ ቅዱስ የታተመ ወይም የተዘጋ መጽሐፍ ነው። ክርስቶስን ማዕከል በማድረግ ያንብቡት ምክንያቱም እስከዛሬ ከተነገሩት ታሪኮች ሁሉ የላቀ ታሪክ ነውና። መጽሐፍ ቅዱስ ለህይወት መመሪያ ማኑዋልነት ብቻ በሚውልብት ጊዜ ዋጋን ይቀንሳል። እንደ ሐዋርያት - እና እንደ ጌታ ኢየሱስም አባባል - መጽሐፍ ቅዱስ ኢየሱስ ክርስቶስ እንደ ማዕከላዊ ገጸ-ባህሪይ አድርጋን ስናነበው አስደናቂ ሆኖ የሚታይ የእግዚአብሄር ትዕይንት ነው።
~ ሚካኤል ሆርተን. ክሪስታል ክርስትና. ግራንድ ራፒድስ, ሚኢ: ቤከር ቡክቸሮች, 2008, ገጽ 142
*ደቀመዛሙርት - ደቀ መዝሙር የኢየሱስ ተ ወይም ተከታይ ነው:: እያንዳንዱ ክርስቲያን ደቀ መዝሙር ነው፡፡ አንዳንድ ጊዜ “ደቀ መዝሙር” የሚለው ቃል ኢየሱስ በምድራዊ አገልግሎቱ ለመሳተፍ የመረጣቸውን አሥራ ሁለት ሰዎች ለመጥቀስ ጥቅም ላይ ይውላል፡፡ *ቤተክርስትያን - ቤተክርስቲያን ኢየሱስ ጌታ መሆኑን አምነው የተቀበሉና የሚመሰክሩ፣ ፈቃዱ በምድር ላይ የተሸከሙ፣ ያለፈውን የአሁንንና የወደፊቱን በታሪክ ውስጥ በየስፍራው በየዘመናቱ እና በምድር ላይ ያሉትን ሁሉ ያጠቃለለ የእግዚአብሔር ህዝብ ማኅበረሰብ ነው፡፡
Made with FlippingBook - Online magazine maker