Fight the Good Fight of Faith, Amharic Edition
ትምህርት 1 ራሳችንን የምናገኝበት የህይወት መድብል • 19
ራሳችንን የምናገኝበት የህይወት መድብል፦ ታሪካችን በእግዚአብሔር ታሪክ ውስጥ ትምህርት 1 የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት የሚከተሉትን ጥቅሶች ያንብቡ እና ከእያንዳንዱ የመጽሐፍ ቅዱስ ትምህርት ጋር የተያያዙትን ጥያቄዎች አጠር ያለ መልስ ይስጡ።
1. ዓጽናፈ ዓለሙን ሁሉን የፈጠረ ጌታ እግዚአብሔር አምላክ ብቻውን እግዚአሄር ነው። ዘፍጥረት 1፡1-3፡15 ን ያንብቡ።
ሀ. በዚህ ታሪክ ውስጥ እግዚአብሔር ምን ድርሻ አለው?
ለ. አዳምና ሔዋን በዚህ ታሪክ ውስጥ ምን ድርሻ ነበራቸው?
ሐ. እባቡ በዚህ ታሪክ ውስጥ ምን ድርሻ አለው?
2. ሁሉም የሰው ልጆች በእግዚአብሔር ፈቃድ እና ኃይል አማካይነት የተፈጠሩና የሚኖሩ ናቸው- የሐዋርያት ሥራ 17፡24-31ን ያንብቡ። ጳውሎስ ለአቴናውያን ስለ እግዚአብሔር ታሪክ በሚያቀርብበት ጊዜ የተናገራቸውን ቢያንስ ሦስት ነገሮችን ዘርዝሩ።
3. እግዚአብሔር ለሰው ልጆች ሁሉ በፍጥረቱ በኩል በእስራኤል ነቢያት በኩል በመጨረሻም በዘመን ፍፃሜ በኢየሱስ ክርስቶስ በኩል ተናግሮ ነበር። ዕብራውያን 1፡1-4 ያንብቡ
ሀ. ጸሐፊው እግዚአብሔር ለሰው ልጆች የተናገረበትን መንገድ እንዴት ይገልጸዋል?
ለ. ጸሐፊው እግዚአብሔር እኛን በጊታ በኢየሱስ ክርስቶስ በኩል ሲናገረን ለዕብራውያን ምን ያህል አስፈላጊ ነው?
4. እግዚአብሔር ሰው በመሆንና በምድር ላይ በመኖር ታሪኩን ተቀላቅሏል! ዮሐንስ 1፡1-14ን አንብብ።
ሀ. “ቃል” ማን ነው? ከእግዚአብሄር አምላክ ጋርስ ያለው ዝምድና ወይም ግንኙነት ምንድን ነው?
ለ. ቃል ከመላው ፍጥረት ጋርስ ያለው ግንኙነት ምንድን ነው?
ሐ. በቃሉ ለሚያምኑ ሁሉ ምን ይቀበላሉ እንዲሁም እንዴት ‘ይወለዳሉ’?
Made with FlippingBook - Online magazine maker