Fight the Good Fight of Faith, Amharic Edition
26 • መልካሙን የእምነት ገድል ተጋደሉ
በዚህ ጥናት ቃልህንና መመሪያህን እንድቀበል አስተምረኝ፡፡ ይህንን ሁሉ ጌታዬና አዳኜ በሆነው በጌታ በኢየሱስ ክርስቶስ ብርቱ ስም እጠይቅሃለሁ አሜን!
1. “ዲያቢሎስ ለምን እኛን ይጠላናል፤ እኛ ምንም ነገር አላደረግነው አድርገናል እንዴ?” ለአዲስ አማኞች በተዘጋጅ አነስተኛ የቡድን የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት ላይ አዲስ በጊታ ያመኑ ሕፃናት ክርስቲያኖች ከመፅሃፍ ቅዱስ አስተማሪ ጋር የቡድን ጥናታቸውን እየተካፈሉ ነበር። በጥናቱ ወቅት የመጀመሪያዎቹ ሰብዓዊ ጥንዶች አዳምና ሔዋንን ሰይጣን በውሸትና በሽንገላ እንዴት እንዳታላቸውና ኃጢአት ሊሰሩ እንደቻሉ አወቁ። ከተማሪዎቹ አንዱ አስተማሪውን “እኔ አልገባኝም። ዲያቢሎስ ለአዳምና ለሔዋን በመዋሸት ወደ ችግር መድረስ እና ለሁሉም ነገር መደፍረስ እና መረበሽ ምክንያት ያደረጋቸው እነርሱ ምን ስላደረጉት ነው? እነርሱ በእርሱ ላይ ምን አድርገውበታል? ሰይጣን ሰዎችን በጣም የሚጠላው ለምንድን ነው? “ ብሎ ይጠይቅ ነበር። በአሁኑ ጊዜ ስለ መጽሐፍ ቅዱስ እና ስለ እግዚአብሄር ስራ ታሪክ በምታውቀው መሰረት መፅሃፍ ቅዱስ ዲያቢሎስ ሰዎችን እጅግ የሚጠላቸው፣ የሚሸነግላቸው የሚያታልላቸው መከራ የሚያበዛባቸው ለምን እንደሆነ ይናገራል? ከመጀመሪያው አንስቶ እንዲህ ያደረገው ለምንድን ነው? 2. “እርግጠኛ አይደለሁም ቢያነስ አሁን ባለኝ ደረጃ እኔ ሁሉንም ነገር ለመቀበል ዝግጁ ነኝ ብዬ አልገምትም።” ማርሻ ስለ በጌታ ስለሚገኘው የዘለአለም ህይወት የምስራቹን ወንጌል ከዘመዷ ከራልፍ ጋር ሲነጋገሩ ሳታውቅ ምን ማድረግ እንዳለበት በማታውቀው ነገር ውስጥ ገባች። ራልፍ እግዚአብሄር ያዘጋጀው የዘላልም ህይወት በረከት መልካምና ያማረ እንደሆነ አምናለሁ ነገር ግን ከሃጢአት ወደ እግዚአብሔር መዞር/ መመለስ/ የሚለው ሃሳብ ግን አይመቸኝም (ምክኒያቱም ራልፍ በኢነተርኔት መርብ በሚደረግ የቁማር ጨዋታ እንዲሁም አንዳንድ አጋንንታዊ ንክኪነት ካላቸው የአዕምሮ ስነ-ጥበባዊ ተግባሮች ውስጥ ተካፋይ ነበርና)። ማርሻ ስለ ክርስቶስ ስራና ፍቅር ምስክርነትን ሲሰጥ ራልፍ እንዲህ አለ “እግዚአብሄር አምላክ ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስን ልኮ ስለ እኛ መስዋዕት በመሆኑ እኛን ምን ያህል እንደሚወደው በእርግጥ አይቻለሁ - አስገራሚም ነገር ነው። ነገር ግን በእርግጠኝነት የምነግርህ አንድ ነገር ቢኖር አሁን ህይወቴን ለእርሱ መስጠት እችላለሁ ብዬ አላምንም፤ በተለይም ደግሞ ሁሉንም ነገር መለወጥ እና አሁን የምሰራቸውን ነገሮች መተው እንዳለብኝ ሳስብ ያ ለእኔ በጣም ከባድ ነው። ለእኔ በጌታ በኢየሱስ ማመን ብቻ በቂ አይሆንም? ለምን ከኃጢያቶቼ ንስሀ መግባትና መመለስ ግድ ይሆናል? “ለምን እንደዚህ ማድረግ ይጠበቅብኛል? እንደዚህ ላለው እጅግ የከበረ መሰጠት ዝግጁ ነኝ ብዬ አላስብም። ንስሃውን ማስወገድ አሊያም ማስቀረት የሚቻልበት ሌላ መንገድ አለ? “ ማርሻ ለእነዚህ ጉዳዮች ምላሽ መስጠት ያለበት እንዴት ነው? - ለመዳን ሲሉ ከኃጢአት ንስሀ መግባት አለብን? ያብራሩ። 3. “አሁን የጌታ ኢየሱስ ደቀ መዝሙር በመሆንዎ የጠላት ዒላማ ሆነዋል።” ብዙ ሰዎች የክርስትናን እምነት እንደ እግዚአብሔር ፍቅርና ፀጋ ብቻ አድረገው ይመለከታሉ ነገር ግን ክርስትና የእግዚአብሄር ወገን ሆነን በእግዚአብሄር ጦርነት ውስጥ የምንሳተፍ መሆናችንን በጥልቀት የተርዱና የተቀበሉ ጥቂቶች ናቸው። እውነታው ግን አንድ ሰው ንስሃ ገብቶ በጌታ በኢየሱስ ክርስቶስ በሚያምንበት ጊዜ በታላቁ ጦርነት ውስጥ አንድ ክርስቲያን ጸሓፊ “የሁሉም ጦርነቶች እናት” ብሎ በሚጠራው ጦርነት ውስጥ ይገባል ወይም ጦርነቱን ይቀላቀላል። “ለክርስቶስ እና ለመንግስቱ” አዎን! ባሉበት በዚያ ጊዜ ለዚህ ዓለም ፈተናዎች ለኀጢአተኛው ባህሪያችን እና ውስጣዊ ስሜቶቻችን እንዲሁም ለጠላት ውሸት “አምቢ ወይም አይሆንም!” ማለታችን ጦርነታችን የጦርነቱ መጀመሪያ ነው። አብዛኛዎቹ እነዚህ ውሸቶች የእኛ ማንነት ቀርፀውታል እኛ በእነዚህ ሃሰቶች በህይወታችን ዘመን ሁሉ ስናምን ኖረናል። በመሆኑም ክርስቲያን መሆን የክርስቶስ ወታደር መሆን ማለት ነው የእግዚአብሔር ጠላቶችም ዒላማ መሆን ማለት ነው።
ግንኙነት
Made with FlippingBook - Online magazine maker