Fight the Good Fight of Faith, Amharic Edition

28 • መልካሙን የእምነት ገድል ተጋደሉ

ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስን እንደ አዳኝ እና ጌታ መቀበል ማለት የክርስቶስን ሠራዊትን ማቀላቀል ማለት ነው። ብናውቀውም ባናውቀውም ለጦርነቱ ተመርጠዋል።

~ ጆን ዋይት “ግብግቡ’’ Downers Grove, IL: InterVarsity Press, 1976, p. 217

ወዶ ዘማችነታችን: -ዘመን ጠገብ በሆነው በዓጽናፈ ዓለም ግጭት ውስጥ ያለንን ሚና መቀበል ትምህርት 2 የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት የሚከተሉትን ጥቅሶች ያንብቡ እና ከእያንዳንዱ የመጽሐፍ ቅዱሳዊ ትምህርት ጋር የተያያዙትን ሃሳቦችን አጠር ያለ መልስ ይስጡ።

1. ቃል ሥጋ ሆነ ለሚያምኑትም ዘላለማዊ መዳንን ያቀርባል። ዮሐንስ 1 10-14ን አንብብ።

ሀ. በዮሐንስ ወንጌል መሠረት ቃል የተባለው እርሱ ማን ነው? ከእግዚአብሔር አብ ጋር ያለው ግንኙነትስ ምንድን ነው?

ለ. ይህ ቃል ከመጥምቁ ዮሐንስ ጋር ያለው ግንኙነት ምን ነበር? ከዓለም ጋር ያለው ግንኙነትስ ምንድን ነው?

ሐ. እግዚአብሔር ሰዎችን የእርሱ ልጆች የመሆን መብት እንዴት ይሰጣቸዋል?

መ. የእግዚአብሔር ልጆች የምንሆነው እንዴት ነው? (ትክክለኛውን መልስ ይምረጡ): i. በደም የተወለደ ወይም ተፈጥሯዊ መውለድ ii. በሰዎች ፈቃድ ወይም በባልም ውሳኔ የተወለደ iii. ከእግዚአብሔር ተወለደ

2. በእግዚአብሔር ጸጋ አማካኝነት ከኃጢአትና ከሞት መዳንን በእምነት በኩል ተሰጥቶናል። ኤፌሶን 21-10ን ያንብቡ።

ሀ. ሐዋርያው* የሰው ዘር ንስሐ ከመግባታቸውና ከማመናቸው በፊት ከሰይጣን (የአየር ላይ መንፈስ አለቃ) ጋር ያላቸው ግንኙነት እንዴት ይገልፀዋል?

*ሐዋርያው ​- ሐዋርያ ማለት “የተላከ” ማለት ነው። ይህ ቃል በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በሁለት መንገድ ጥቅም ላይ ውሏል። ብዙውን ጊዜ ልክ እንደዚሁ, ቃሉ የሚያመለክተው ኢየሱስ ራሱ በምድራዊ አገልግሎቱን ዘመን አብረውት የነበሩትን 12 ደቀመዛሙርት እና እንደ ጳውሎስ ዓይነት ሰው በሐዋርያት ሥራ ምዕራፍ 9 ውስጥ ከኢየሱስ ክርስቶስ ግላዊ ተልዕኮን ለተቀበለው ነው:: የሐዋርያቱ የዓይን ምስክርነት ለእኛ ወሳኝ ነው ምክንያቱም የእነሱ ምስክርነት ስለ ክርስቶስ የምናውቀውን ሁሉ የሚገልጽ ነው (1 ዮሐንስ 1.1-4 እና 2 ኛ ጴጥሮስ 1.16-18ን ተመልከት)። ለዚህ ነው የኒቂያው የሃይማኖት መግለጫ እምነታችን “ሐዋርያዊ” ብሎ ሲናገር የእኛ መጽሐፍ ቅዱስ እና የሰው ታሪክን የምንተረጉመው በሐዋርያት ትምህርት ላይ መሰረት በማድረግ ነው፡፡ በሁለተኛው መንገድ “ሐዋርያ” የሚለው ቃል ጥቅም ላይ ውሏል (ለምሳሌ ኤፌ 4:11) ይህም በመንፈስ ቅዱስ ሰጦታ ለተለየ ተግባር ወይም ተልዕኮ ለተላኩት ነው፡፡ ዛሬ እኛ “ሚስዮናውያን” ብለን እንጠራቸዋለን ማለትም ለተወሰኑ ዓላማዎች እንደ ተላኩ ለምሳሌ አብያተ ክርስቲያናትን ለመትከልና ለመሳሰሉት።

Made with FlippingBook - Online magazine maker