Fight the Good Fight of Faith, Amharic Edition
32 • መልካሙን የእምነት ገድል ተጋደሉ
i. አሁን መንፈስ ቅዱስን የተቀበልን እኛ ለኃጢያት መሰጠት የለብንም፡፡
ii. እኛ በመንፈስ አማካኝነት የእግዚአብሔር ቤተሰቦች ለመሆን ተወልደናል፡፡
iii. እኛ የእግዚአብሔር ወራሾች ነን፥ አብረንም ደግሞ መከራ ብንቀበል ከክርስቶስ ጋር አብረን ወራሾች ነን።
9. እግዚአብሔር በዲያቢሎስ እና በኃጢአት ላይ ክርስቶስ ያደረገውን ድል የምስራቹን እንዲናገሩ መልእክተኞችን ወደ ዓለም ልኳል። የሐዋርያት ሥራ 26፡12-18ን አንብበው ባዶ ቦታዎቹን ይሙሉ። ጳውሎስ ከኢየሱስ ክርስቶስ መገለጥን ሲቀበል ጌታ ኢየሱስ ምን እንዲያደርግ ሾመው?
ሀ. ለሚያያቸው ነገሮች አገልጋይ እና _____________ (ቁ 16)
ለ. የሰዎች ዓይን ይከፍት ዘንድ ከ ___________________ ወደ ብርሃንና ወደ ከ __________________ ወደ እግዚአብሔር የኃጢአትንም _________________ በተቀደሱት መካከል ___________________ ርስትን ያገኙ ዘንድ (ቁ. 18)።
ወደ እግዚአብሄር የተመለሰ(ንስሃ) የገባና ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ከሙታን እንደተነሳና ጌታ እንደሆነ የተቀበለ (እምነት)ሰው ሁሉ በእሱ ድኗል - ይቅር ተብሏል በእግዚአብሄር ቤተሰብነት ውስጥ ተቀላቅሏል። ይህ የእግዚአብሄር ልጅ ለመሆን የቀረበ ጥሪ ለዚህን ዓለም እና ለኃጢአት ያለንን ታማኝነታችንን ክደን ለክርስቶስ እና ለእርሱ መንግሥት ታማኝ ለመሆን ተጠርተናል ማለት ነው። ማመን ማለት ከዚህ ዓለም ወደ እግዚአብሔር ዞር ማለት፣ ለሌላ ጌታ አዲስ መንግሥት እና አዲስ ህይወት ታማኝ መሆን ማለት ነው። ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ የመጣው የሰይጣንን ሥራ ለማጥፋት የሰውን ዘር ከእግዚአብሔር ጋር ወደ ትክክለኛው ግንኙነት ለመመለስ እና በቅርቡ ሲመለስ በመንግሥቱ ግዛት ስራዓት ፍጥረትን ሁሉ ወደ ቀድሞ ሁኔታቸው እንዲመልሳቸው ነው። ድነትን ያገኘነው በእግዚአብሔር ፀጋ እንጂ ለእርሱ ህግ በመታዘዛችን ወይም በራሳችን መልካም ማንነት ወይም በመልካም ስራዎቻችን ምክንያት አይደለም። እኛ ከእግዚአብሔር ጋር ትክክለኛ ህብረት ሊኖረን የቻለው በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ምትክነት (“በእኛ ቦታ በመሞቱ”) እና በእርሱ ምህረት ብቻ ነው። አሁን ድነናል በአንፃሩ ከኃጢአት ከክፉ እና ከጨለማ መንግሥታት ጋር በመዋጋት ላይ እንገኛለን። እንደ እውነቱ ከሆነ ለመዳን የቀረበው ግብዣና ጥሪ የጌታን የተወደደው ሠራዊት ለመቀላቀል እና ከዓለም ከአሮጌው የኃጢአት ተፈጥሮ እና ከሰይጣን ጋር ለመዋጋት የቀረበም ጥሪ ነው። እኛ በጌታ በኢየሱስ ክርስቶስ ካመንን በኋላ እግዚአብሔር በእኛ ውስጥ መኖሪያውን እንዲያደርግ ብርታት መመሪያን እና እግዚአብሔርን ማክበርን እንዲሁም ክርስቶስን ማገልገልና የእርሱን ሥራ እንድንሰራ በመንፈስ ቅዱስ አትሞናል። መንፈስ ቅዱስ ኢየሱስ በሚመለስበት ጊዜ ወደ እኛ የሚያመጣውን የእግዚአብሔር ሙሉ ስጦታ ቀብድ ክፍያ (መያዣ) ነው። መንፈስ ቅዱስ በክርስቶስ ላለን የሚመጣ ውርስ ዋስትናችን ሆኗል። የእግዚአብሔር ደጋግ ስጦታዎችና በረከቶች ማለትም የኃጢአት ይቅርታን ማግኘት ከዲያቢሎስ እና ከጨለማ መንግስት መዳን እንዲሁም የክርስትናን ሕይወት ስንኖር የእግዚአብሔርን ፈቃድ ለመታዘዝ እንድንችል ኃይል ማግኘትን በሙሉ በመንፈስ ቅዱስ በኩል እውን ሆነዋል።
ማጠቃለያ
Made with FlippingBook - Online magazine maker