Fight the Good Fight of Faith, Amharic Edition
34 • መልካሙን የእምነት ገድል ተጋደሉ
ሐጢአታቸው ከእንሱ “መወገዱን” ዋስትና ማጣት ብቻ አይደለም፤ ነገር ግን ሁሉም ነገር በመጀመሪያ በአዕምሯቸው ውስጥ እርግጠኛ መሆን አለመሆኑን ይጠራጠራሉ። ከዚህ በላይ ያሉትን መጽሐፍ ቅዱሳዊ ጽሑፎች መመርመራችሁ እና ማጥናታችሁ እንደነዚህ ዓይነት ቀስቃሽና ቀጣይነት ያለውን ጥርጣሬ የሚፈጠርባቸውን ሰዎች ችግር ለመፍታት እንዴት ሊያግዛችሁ ይችላል? አንዳንድ አዳዲስ አማኞች በእያንዳንዱ ቀን ሊገጥማቸውና ሊሰማቸው ከሚችለው የስሜት መዋዠቅ ባሻገር መዳናቸውን እንዲያረጋግጡ እንዴት ልትረዷቸው ትችላላችሁ (1 ዮሐንስ 5.11-13ን ተመልከቱ)? 3. “የሚገርም ነው። እኔ አሁን በእግዚአብሄር ጸጋ ድነት ውስጥ ስለምኖር ሁሉ ማድረግ እችላለሁ። እኔ ነጻ ነኝ!” በአንድ ወቅት አንድ አዲስ አማኝ መጽሐፍ ቅዱስ ስለ እግዚአብሄር ፀጋ ስለ ክርስቶስ ጽድቅ እና የዘለአለም ህይወት የሚሰጠውን ትምህርት ከተመለከተ በኋላ የተናገረው ነው። ትሑት እና አመስጋኝ ከመሆን ይልቅ እውቀቱን በስህተትና በዕብሪተኝነት በተሳሳተ መንገድ ተመልክቶት ድምዳሜውን አጣመመ። ይህንንም የተወላገድ መረዳቱን ከወዳጆቹ ጋር መጋራት ጀመረ “እግዚአብሔር ይወደናል እና በጸጋው አድኖናል፣ ስለዚህም ስለ እኛ አኗኗር መጨነቅ አይኖርብንም። እኛ የምናደርገውን ሁሉ እርሱ ይቅር ይለናል ይቀበለናልም። እኛ በእርሱ ዘንድ ተቀባይነት የሚኖረን እኛ በምንሰራው ስራ መሠረት ሳይሆን በኢየሱስ በኩል ነው! ስልዚህ ስለምንኖረ ኑሮ መጨነቅ የለብንም” ይህ አዲስ ወንድማችን በክርስቶስ ያገኘነውን አዲስ ህይወት እንዴት መኖር እንዳለብን ስለሚናገረው የእግዚአብሄር ሃሳብ ጋር በተሳሳተ መንገድ የተረዳው እንዴት ነው? በጌታ ከሆንን በኋላ አሁን እንዴት መኖር እንዳለብን እውነተኛ መረዳት ምንድነው? አንድ አማኝ በእግዚአብሔር አስደናቂ ታሪክ ውስጥ ለመጓዝ የመጀመሪያው እና ትርጉም ካላቸው ነገሮች መካከል አንዱ ሁልጊዜ በከፍተኛ ሰልፍ እና በመያቋርጥ ውጊያ ውስጥ ተፋላሚ መሆናቸውን መረዳት ነው። እንደ እውነቱ ከሆነ ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስን ስንቀበል ምንም ውጫዊ ነጎድጓድ ወይም አካላዊ ለውጥ የለም (ቢያንስ ቢያንስ በተለምዶ!) ሁሉም ነገር እንደ ነበረ ሊመስል ይችላል። ይሁን እንጂ እውነታው ግን ሁሉም ነገር ተለውጧል። እኛ ከጨለማው ስልጣን አምልጠናል፣ ከኃጢአታችን ሁሉ ይቅር ተብለናል፣ የእግዚአበሄር ልጆች እንድንሆን አዲስ ልደትን አግኝተናል የእግዚአበሄርም ቤተሰብ ሆነናል፣ በመንግስቱ ውስጥም ለመጋደል የውጊያውን ሰራዊት ተቀላቅለናል። የእግዚአብሄ ቃለ እንደሚመሰክረው እኛ በክርስቶስ አዲስ ፈጠረቶች ነን፤ አሮጌው ሁሉ አለፏል ሁሉም አዲስ ሆኗል (2 ቆሮ 5፡17)። በመሆኑም አሁን የውጊያን/የተጋድሎ/ መንፈስን ለመላበስ ወስኑ፣ ለመንፈሳዊ ብርታታችሁ በጌታና በመንፈስ ቅዱስ ተደገፉ፣ ከክርስቶስ ጋር በየዕለቱ ስትራመዱ ለዕርዳታ ወደ እግዚአብሔር ጸልዩ፣ እንዲሁም በልባችህ በአዕምሮአችሁን በነፈሳችህ በክፉው ቀን ሁሉን ፈፅማችሁ ለመቆም እንድትችሉ ጽኑ። እግዚአብሄር ድልን ሊሰጣችሁ ቃል ገብቷልና (1 ቆሮ 15፡57) ምክንያቱም በእናንተ ውስጥ ያለው በዓለም ካሉት ይልቅ ይበልጣልና (1 ኛ ዮሐንስ 4፡4)። አሁን እናንተ ለጌታ ናችሁ በመሆኑም በስጋቶች በውሸቶችና በማጭበርበሮች ከተሞላው ከቀድሞው ህይወታችሁ ጋር ራሳቸሁን ማዛመድ የለባቸሁም። እናንተ በክርስቶስ አዲስ ፍጥረት በመሆን የእግዚአብሔር ልጅ ሆናችኋል እናም ሆን ብላቸሁ በዚህ በአዲሱ ማነነታቸሁና ልጅነታቸህ እንደ አዲስ ሰው ማሰብ መንቀሳቀስ እና መናገር ጀምሩ። እራችሁን በተዕግስት ተብቁ ምክንያቱም የእግዚአብሔርን አዳዲስ መንገዶች መማርና እግዚአበሄር እንድትሆኑ የፈለገውን አዲስ ሰው መሆን ትዕግሰትና ጊዜ ይወስዳልና።
ማዛመድ
በዚህ አዲስ ማንነት ውስጥ ለመኖር እንዲረዳችሁ እግዚአብሔርን ጠይቁት፤ ይህ እግዚአብሔር የሰራው አዲስ ማንነት ካለፈው ካሮጌው ህይወት ምኞት ነፃ የወጣ፣ በአዕምሮአችሁ መታደስ
Made with FlippingBook - Online magazine maker