Fight the Good Fight of Faith, Amharic Edition
8 • መልካሙን የእምነት ገድል ተጋደሉ
ትምህርት 1 ራሳችንን የምናገኝበት የህይወት መድብል - የእኛን ታሪክ ከእግዚአብሔር ታሪክ ጋር ማስተሳሰር የሚለውን ሃሳብ ያስተምራል። ይህ ትምህርት ዓጽናፈ ዓለሙን ሁሉ የፈጠረ አምላክ ሁሉን ቻይ ጌታ ብቸኛ እውነተኛ እና የዘላለምም አምላክ እንደሆነና በሶስት አካል ውስጥ አባት፣ ልጅ እና መንፈስ ቅዱስ እውን መሆኑን ያሳውቀናለ። እሱ ሁሉንም ነገር ማለትም- የሚታየውንና የማይታይውን ሁሉ የፈጠረ እንዲሁም ሰዎችን በራሱ መልክና አምሳል የፈጠረ ነው። ይህ ትምህርት የሰይጣንን እና የመጀመሪያዎቹን ሰብዓዊ ጥንዶች፣ የአዳምን እና ሔዋንን ዓመፅ እና በነርሱም አለመታዘዝ ምክንያት ፍጥረት ሁሉ እንዴት እንደተረገመ ያብራራል። ይሁን እንጂ እግዚአብሔር ደግሞ ክፋትን ሁሉ የሚያሸንፍ እና ሁሉንም ለእግዚአብሔር ክብር የሚመልስ የአዳኝን እንደሚልክ ተስፋ እንደሰጠንም ያሳያል። ትምሕርት 2 ወዶ ዘማችነታችን፦ በአጽናፈ አለሙ ዘመን ጠገብ ግጭት ውስጥ ያልንን ድርሻ መቀበል የሚለው ትምህርት የናዝሬቱ ኢየሱስ ሰይጣንን እንዴት እንዳሸነፈና ከኃጢአት ነፃ በሆነ ህይወቱ እና በእኛ ምትክ በመሞቱ ከኃጢአትና ከእርግማን እንዴት ነፃ እንዳወጣን ያብራራል። አሁን ንስሃ በመግባት (ከኃጢአታችን ወደ እግዚአብሔር በመመለስ) እና በእምነት (በኢየሱስ ሥራ ላይ በእርጋጥ በማመን) ወደ እግዚአብሔር መንግሥት እንገባለን:: በጸጋው ያድነናል ፤ በክርስቶስ አካል ውስጥ እንጠመቃለን፤ እንዲሁም በክርስትና ህይወታችን እኛን ለመርዳት መንፈስ ቅዱስ ይሰጠናል፡፡ ትምሕርት 3 የምናገኘው መግቢያ : - ህይወታችንን በክርስቶስ ከእግዚአብሔር ህይወት ጋር ማያያዝ የሚለው ትምህርት ከጌታ ከኢየሱስ ጋር እንዴት በእምነት እንደተሳሰርን ያስተምራል (ማለትም አሁን እኛ “በክርስቶስ” ነን)፡፡ በዚህ ትስስር ወይም ህብረት ምክንያት ጌታ ኢየሱስ የሆነውን እና የሚሰጠውን ሁሉ ትቀበላላችሁ ትለማመዳላችሁም፡፡ በእግዚአብሔር መንፈስ አማካይነት ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ የማዕዘን ራስ ድንጋይ ወደሆነበት ሐዋርያትና ነቢያት መሰረት ወደ ሆኑበት የእርሱ ቤተሰብ ወይም ቤተ ክርስቲያን አባላት እንሆናለን፡፡ እያንዳንዱ የአጥቢያ ማኅበረ ምዕመናም የሰማይን ፍላጎቶች የሚያገለግል የእግዚአብሔር መንግሥት ኤምባሲ ሆኖ ያገለግላል ይወከላል፡፡ እኛ አማኞችም የዚህ መንግስት አምባሳደሮች እና ወኪሎች ሆነን እናገለግላለን፡፡ ትምሕርት 4 በዚህ ትምህርት የተቀበልነው ስጦታ: -በመልካሙ የእምነት ተጋድሎ ውስጥ የመንፈስ ቅዱስ ሚና የሚለውን እንነጋገራለን፡፡ ይህ ትምህርት መንፈስ ቅዱስ በእያንዳንዱ አማኝ ውስጥ እንዴት እንደሚያድር፣ እና ለቤተ ክርስቲያን አገልግሎት ለእያንዳንዱን ስጦታ የሚሰጥበትን መንገድ ያሳያል፡፡ መንፈስ ቅዱስ ለእያንዳንዳቸን እንደሚሰጠን ዕድል መመሪያ እና ብርታት መጠን ከሌሎች አማኞች ጋር ስጦታችንን መለማመድ እንድንችል በክርስቶስ ነፃ ወጥተናል፡፡ እያንዳንዱ አማኝ ኅብረቱን በአንድነትና በፍቅር በሚያገለግልበት ወቅት ሁላችን እንደ አካል ተያይዘን እናድጋለን፡፡ በትምህርት 5 ውስጥ ስለምናሳየው ልዕቀት: - በዚህ ዓለም እንደ እግዚአብሔር ቅዱሳን እና የክርስቶስ አምባሳደሮች መኖር የሚለውን እንመለከታለን። ሁላችንም እንደ ተወደዱ ልጆች የእርሱን ምሳሌ እንድንከተል የተጠራን መሆናችንን እናያለን፡፡ በክርስቶስ እኛ የእግዚአብሄር ቅዱሳን (ቅዱስ) ተብለን በሰዎች ሁሉ ፊት ቅዱሳንና የእርሱን በጎነት በመናገር እግዚአብሄርን እንድንወክል ተጠርተናል፡፡ እንዲሁም እንደ ክርስቶስ አምባሳደሮቹ፡ ለጓደኞቻችን፤ ለቤተሰቦቻችን እና ለሌሎች ጎረቤቶቻችን የመዳንን መልካም ዜና በማካፈል እና መልካም የፍቅር ስራዎችን በመስራት፤ ለክርስቶስ መስራት እና ለሌሎች አገልግሎት በመስጠት እንድናገለግል ተጠርተናል፡፡ ትምህርት 6 የምንፈለገው መታነጽ: - በክርስቶስ አካል ውስጥ እርስ በእርስ መተናነጽ በሚለው ትምህርት ውስጥ የክርስቲያን ሕይወት ፅንሰ ሃሳብ በህበረት ውስጥ ለመኖር የተቀየሰ እንደ እግዚአብሔር ቤተሰቦች አብሮ ለማደግ የክርስቶስ አካል እና የመንፈስ ቅዱስ ቤተመቅደስ እንደሆነ እንዳስሳለን።፡ በአጥቢያ ቤተክርስቲያን እና በትንንሽ ቡድኖች ውስጥ ከሌሎች አማኞች ጋር ተያይዘን
Made with FlippingBook - Online magazine maker