Fight the Good Fight of Faith, Amharic Edition
92 • መልካሙን የእምነት ገድል ተጋደሉ
ከዚህ በታች በተመለከቱት ፅሁፎች ላይ በመመርኮዝ የሚከተሉትን ክርክሮች እና ጽንሰ ሐሳቦች ያንብቡ እና ያብራሩ እና መልስም ይስጡ
የናሙና ጥናቶች
1. “ ‘በእምነት ጸንተህ መቆም ’ ማለት ምን ማለት እንደሆነ ለመረዳት እሞክራለሁ፣ ነገር ግን በእርግጠኛ እንዳገኘሁት አይሰማኝም።” ከጓደኞቻቸው ጋር መጽሐፍ ቅዱስን በጥልቀት ካጠና በኋላ አንድ ወጣት ክርስቲያን በ1ኛ ጴጥ 5፡8-9 ላይ ያለውን የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል ትርጉም ታሰላሰል ነበር፡ ሁላችሁም በመጠን ኑሩ ሁልጊዜም የነቃችሁ ሁኑ። ባላጋራችሁ ዲያብሎስ የሚውጠውን ፈልጎ እንደሚያገሣ አንበሳ ይዞራልና። ዲያቢሎስ ሰይጣንን በእምነት ጸንታችሁ ልትቃወሙት ይገባል።በተጨማሪም በተመሳሳይ ሁኔታ እንዲህ ዓይነቱ መከራ በመላው ዓለም ባሉ አማኞች ሁሉ እየታየ እንደሆነ ማወቅ ይገባችኋል። በዚህ ክፍል ላይ ተመስርታ በእምነታችሁ መጽናት የሚለውን ሃሳብ ምን ማለት እንደሆነ ለመረዳት ጥረት ታደርግ ነበር። በመጽሐፍ ቅዱስ ጥናታቸው ወቅት መሪው በዚህ ጽሑፍ ውስጥ “መቃወም” የሚለው ቃል የግሪክ ቃል ትርጓሜው ኤውንቲስት ሲሆን በኤፌሶን 6፡11-13 እና በያዕቆብ 4፡7 ውስጥ ጥቅም ላይ ውሏል ብሎ ሲናገር ሰምታ ነበር። ትርጉሙም ምንም እንኳን ነገሮች ከእውቀታችን ተቃራኒዎች ቢመስሉም በታማኝነት መጽናት፣ ወይም በእግዚአብሄርን ቃል መታመን ማለት ነው። እሷም አስቸጋሪ በሆኑ ጥያቄዎች እየታገለች ነበርና፤ “ይህ ማለት እኔ ልጠራጠር አልችልም ወይም የለብኝም ማለት ነው? ተስፋ የምቆርጥ ብሆንስ? ምናልባት ብንሸራተትና ብወድቅስ-እንደገና መመለስ እችላለሁ?”ይህች ወጣት እህት ይህንን ጽንሰ-ሐሳብ እንድትረዳ እንዴት ትመክሯታላችሁ? አንዳንድ አስገራሚ ሃሳቦች አንዱ ምንም እንኳን ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ድል የተቀዳጀ ቢሆንም አማኞች በእምነታቸው ጸንተው የዲያቢሎስን ሽንገላ በመቃወም እንዲቆሙ የግድ አስፈላጊ የሆነበት ምክንያት ነው። በርግጥ ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ በመስቀል ላይ ዲያብሎስን ድል ነስቶታል (ቆላ 2፡ 15) እንዲሁም አማኞች ከበጉ ደም የተነሣ ከምስክራቸውም ቃል የተነሣ እና ነፍሳቸውንም እስከ ሞት ድረስ ባለመውደድ ድል ይነሡታል (ራዕ 12, 9-10)። ታዲያ አሁንም ቢሆን መዋጋት የሚያስፈልጋቸው ለምንድን ነው? ኢየሱስ በመጀመሪያው መምጣቱ የሰይጣንን ሥራውን ካፈረሰ በኋላም እንኳ ጌታ እግዚአብሄር ዲያቢሎስ ህዝቡን እንዲዋጋ ለምን ፈቀደ (1 ዮሐንስ 3፡8)? (ፍንጭ-ኢየሱስም አለ የአገልጋዩ ከጌታው አይበልጥም ዮሐንስ 13፡16)። 3. “እኔ ያልፍኩበትን የሥቃይ ዓይነት እና የልብ ሐዘን ማንም ሊረዳው አይችልም። ማንም !።” አስቸጋሪ ጊዜን፣ ሐዘንን፣ ወይም ውድቀት ሲያጋጥመን የኛ ልዩ እንደሆነ እና እኛ ብቻ እንደሆንን በማሰብ እኛ የምንሄድበት መንገድ ወይም የፈተና ዓይነት የሚያጋጠመው ማንም የለም ብለን እንፈተናለን። የሕመምና የጉዳት ዓይነትኛ ባህሪው ቅርብ እና ግላዊ መሆኑ ነው፤ የእኛ መጎዳትና ትግሎች በጣም አስከፊ ከመሆናቸው የተነሣ ማንም ሰው እኛ የምናልፍበት ፈተናና ጉዳት የሚሰማው አይመስለንም፤ እንዲሁም ማንም ሰው እኛ አሁን ያጋጠመንን የጉዳት፣ የተስፋ መቁረጥ እና የመጨረሻ የመቁሰል ደረጃውን ሊገነዘበው አይችልም ብለን እናስባለን። በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ የሚገኙት በርካታ ጥቅሶች ነገሩ እንዲህ እንዳልሆነ ይጠቁማሉ። እኝ የምንካፈላቸው መከራዎቻች እና አስቸጋሪ ፈትናዎችን በዓለም ዙሪያ ያሉ ሌሎች አማኞች ከሚገጥሟቸው ፈተናዎችና ተግዳሮቶች ጋር ተመሳሳይ ናቸው። ጳውሎስ በቆሮንቶስ ለሚኖሩ ክርስቲያኖች በ 1ኛ ቆሮንቶስ 10፡13 የተናገረውን ተመልከቱ፡ ለሰው ሁሉ ከሚሆነው በቀር ምንም ፈተና አልደረሰባችሁም፤ ነገር ግን ከሚቻላችሁ መጠን ይልቅ ትፈተኑ ዘንድ የማይፈቅድ እግዚአብሔር የታመነ ነው- እርሱ እምነት የሚጣልበት ነው፤ እናም ያንን ፈተና ለመቋቋም ከምትችሉት በላይ እንድትፈተኑ አይፈቅድም፥ ትታገሡም ዘንድ እንድትችሉ 2. “ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስለ እኛ ድልን ከተቀዳጀ በኋላም እንኳን እግዚአብሔር ዲያቢሎስ እኛን እንዲያስቸግር እና እንዲጎዳን ለምን ይፈቅዳል?” ለአዲስ አማኞች ለመረዳት ከሚያስቸግሩ
Made with FlippingBook - Online magazine maker